Etiópia

Tigray.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-19 09:52:12
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተሰርዞ ሕጋዊ ሰውነቱን ያጣው የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ የክልሉን ወቅታዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ያደረገው የአክሱም ስብሰባ፣ በትግራይ ውስጥ ያለውን የፖለቲካ መከፋፈልና የዳግም ጦርነት ሥጋት እንዳባባሰውና ድርጅቱ የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር ውድቅ በማድረግ ከጦርነቱ በፊት የነበረውን የመንግሥትነት መዋቅር ለመመለስ ሊንቀሳቀስ እንደሚችል የሚጠቁሙ ምልክቶች እየታዩ መሆኑን የክልሉ ፖለቲከኞች ገለጹ። ሕወሓት የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባው በጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት ላይ ያተኩራል ብሎ በግልጽ ባይናገርም፣ በቁልፍ አጀንዳዎችና ወቅታዊ የፖለቲካ ዕድገቶች ላይ ‹‹በጥልቀት›› የሚመክር ስብሰባ ሚያዚያ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. መጀመሩን፣ እንዲሁም ተጨባጭ አቅጣጫዎችና ውሳኔዎች እንደሚተላለፉ ለሕዝብ ይፋ ባደረገው አጭር መግለጫ አረጋግጧል። ሪፖርተር ያነጋገራቸው በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች በበኩላቸው፣ ሕወሓት ሚያዚያ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. የጀመረው ይህ ስብሰባ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት ሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ የሥልጣን ዘመን መራዘምን ተከትሎ በተፈጠረው አለመግባባት ላይ ያተኩራል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል። ጉዳዩ በሕወሓትና አሁን ባለው የክልሉ አመራር መካከል ያለውን ሰፊ ልዩነት መሆኑን ያሳየና ፕሬዚዳንቱ በበኩላቸው የሥልጣን ዘመን መራዘሙን አስመልክቶ በክልሉ ውስጥ የሚነሱ ተቃውሞዎችን ‹‹አልቀበልም ማለት መብት...
Politics-77.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-19 03:21:09
መንግሥት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጨምሮ በተለያዩ የኢትዮጵያ ግድቦች የተሳተፉ ባለሙያዎች በአንድ ድርጅት ሥር ሆነው እንዲሠሩ የማድረግ ዕቅድ እንዳለው ተገለጸ፡፡ በመንግሥት በኩል ይኼ ዕቅድ እንዳለ የተገለጸው ‹‹ኢትዮጵያ ትገነባለች፣ ትገነባለችም! ፈጠራ፣ ፍጥነትና ጥራት ለመሠረት ልማት አመራር›› በሚል መሪ ቃል ከሚያዚያ 9 እስከ ነገ ሚያዚያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. እየተካሄደ በሚገኘው የኢትዮጵያ የመሠረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሳምንት መክፈቻ ሥነ ሥርዓት በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ሲካሄድ ነው። በመድረኩ ‹‹እንደ አገር የመሠረተ ልማት ግንባታን እንዴት እንመራለን?›› በሚል መነሻ ሐሳብ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሒደት የታዩ ስኬቶችና የተገኙ ተሞክሮዎች ለቀጣይ ጉዞ እንደ ትምህርት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። በዚህም የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክፍሌ ሆሮ (ኢንጂነር) መንግሥት ህዳሴን ጨምሮ በሌሎች ግድቦች ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎችን በአንድ ድርጅት ሥር አሰባስቦ ልምድ አግኝተው፣ ነፃ ሆነውና ራሳቸውን ችለው፣  ከአገር አቀፍ አልፎ ዓለም አቀፍ ኮንትራክተር እንዲሆኑ ለማድረግ ሐሳብ እንዳለው አስረድተዋል። ይህ እስኪሆን ድጋፍ ይሰጣል ሲሉም ተናግረዋል። ለዚህ ድርጅት መቋቋም መነሻው በኢትዮጵያ ባሉ የግድቦች ሥራ የተስተዋለው አንዱ ችግር፣ የተገኘው የእውቀት ሽግግር ተሰብስቦ...
MOE.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-19 03:20:03
የትምህርት ሚኒስቴር በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በማይመረጡ የትምህርት መስኮች ሲያስተምሩ የነበሩ መምህራን፣ ከተማሪዎች ጋር በመሆን በሚያዋጣቸው ፊልድ መንቀሳቀስ አለባቸው አለ፡፡ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ይህንን የተናገሩት፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የሚኒስቴሩን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ ሪፖርት ሚያዝያ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ሲገመግም ነው፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ባቀረበው ጥያቄ በዩኒቨርሲቲዎች ሒሳብ፣ ሳይንስና ግብርና ትምህርቶች በተማሪዎች እየተመረጡ አለመሆኑን ጠቅሶ፣ ችግሩን ለመፍታት ምን እየተሠራ ነው ሲል ጠይቋል፡፡ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሸ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ፍልስፍና፣ ታሪክ ወይም ሌሎች የትምህርት መስኮች በተማሪዎች ካልተመረጡ መምህራኑም ሥራ ወዳለበት ቦታ ሊሄዱ ይገባል ብለዋል፡፡ ‹‹መምህራንም ሆኑ ሠራተኞች በእኛ አገር አንዴ የያዙትን ቦታ መልቀቅ አይፈልጉም፡፡ እኛ ደግሞ የምንፈልገው በዩኒቨርሲቲዎቻችን ተማሪዎች የትምህርት መስክ እየመረጡ፣ መምህራንም ከአንድ ቦታ ወደ የሚፈልጉት ሌላ ቦታ እንዲሄዱ እንፈልጋለን፤›› በማለት ገልጸዋል፡፡ አክለውም በዩኒቨርሲቲዎች ያለ ምንም ምክንያት ክፍል በማይገቡ መምህራን ላይ በአዲስ አበባ ጭምር ቁጥጥር እናደርጋለን ብለዋል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ሪፖርቱን ተመልክቶ ባቀረበው ጥያቄ፣ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ 12ኛ ክፍል ወደ ትምህርት እንዲመጡ ታቀዶ...
Translate »