Etiópia

Education.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-07-15 04:46:46
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካውንቲንግ (የሒሳብ አያያዝ) ትምህርት አሰጣጣቸውን መከለስና ጊዜው ከደረሰበት ደረጃ ጋር አብሮ እንዲሄድ ማድረግ እንዳለባቸው፣ የኢትዮጵያ የተመሰከረላቸው የሒሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ጥያቄ አቀረበ፡፡ የኢትዮጵያ የተመሰከረላቸው የሒሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ የሒሳብ አያያዝ ቴክኒካዊ ብቃት (Accounting Technician Qualification Ethiopian – ATQE) ሥልጠናን መስጠት የሚያስችል ስምምነት ከ11 የመንግሥትና የግል ተቋማት ጋር ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ተፈራርሟል። በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና የኢትዮጵያ የተመሰከረላቸው የሒሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት የቦርድ አባል ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)፣ የአካውንቲንግ ዘርፍ ትምህርትና በኢትዮጵያ በሥራው ውስጥ ሰፊ ልዩነት እንዳለውና አንድ ሰው ዲግሪ ይዞ ተመርቆ ሥራ ቦታ ሲሄድ የሚያጋጠመው ተጨማሪ ሥልጠና እንደሆነ ገልጸዋል። ከዚህም አንፃር በዘርፉ ያለውን የከፍተኛ ተቋማት ሥርዓተ ትምህርት ቀረብ ብሎ ማየትና ክለሳ በማድረግ ከሙያው ጋር የተናበበ እንዲሆን መሥራት ይገባል ሲሉ አሳስበዋል። እንደ ኬንያ፣ ኡጋንዳና ታንዛኒያ በመሳሰሉ ጎረቤት አገሮች የዘርፉ ሥርዓተ ትምህርት ከሙያው ጋር የተናበበ መሆኑን ተናግረዋል። የእነዚህ አገሮች የሒሳብ ባለሙያዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የሙያ ማኅበራት በጋራ ተቋማት ተቀራርበው በመሥራታቸው ያፈሩት የሠለጠነ የባለሙያ ቁጥር ከኢትዮጵያ እንደሚበልጥ...
Immigration.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-15 04:45:46
የውጭ ዜጎችና ኢትዮጵያውያን በሐሰተኛ ሰነድ የማጭበርበር ድርጊት ተጠያቂ መደረጋቸው ተገልጿል በ2018 በጀት ዓመት ከ1.6 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርቶችን ጨምሮ በተሰጡ አገልግሎቶች ከ42.7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን፣ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ ይህን ያለው ማክሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸሙን ሲገመግም ነው። አግልግሎቱ በበጀት ዓመቱ ከ1.6 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርቶች ለዜጎች መሰጠት መቻሉ በዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረኩ ተነግሯል። በበጀት ዓመቱ 1,046,286 ቪዛዎች፣ ለ32,952 ትውልደ ኢትዮጵያውያን መታወቂያዎች (ቢጫ ካርድ)፣ እንዲሁም ለውጭ ዜጎች 21,163 ጊዜያዊና ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ በመስጠት የተሳካ የዕቅድ አፈጻጸም ማስመዝገቡን አገልግሎቱ ገልጿል። ከፓስፖርት፣ ከቪዛ፣ ለትውልደ ኢትዮጵያዊ ከተሰጡ መታወቂያና ከሌሎች አገልግሎቶች ከ42.7 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አገልግሎቱ አስታውቋል። በበጀት ዓመቱ 433 የውጭ ዜጎችና 4,450 ኢትዮጵያውያን በሐሰተኛ ሰነድ የማጭበርበር ድርጊት መፈጸማቸውን፣ 21 ግለሰቦች ደግሞ በሕገወጥ ድለላ ተግባር ተይዘው ተጠያቂ መደረጋቸው ተገልጿል። ከዚህም ባለፈ 174 ግለሰቦች አስቸኳይ ፓስፖርት በሕገወጥ መንገድ በበይነ መረብ ሲሞሉ መያዛቸውን፣ ከዚህም ጋር በተያያዘ 24 ንግድ ቤቶች እንዲታሸጉ መደረጋቸውን አገልግሎቱ አስታውቋል። በአየርና በየብስ በድንበር አካባቢ...
Translate »