Etiópia

Taxi.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2025-02-06 09:16:17
እነሆ ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ ልንጓዝ ነው። ከረጅም ሠልፍና ጥበቃ በኋላ የተገኘ ዶልፊን ሚኒባስ ታክሲ በወያላው አስተናባሪነት በየተራ ተሳፍረን መቀመጫችን ስንይዝ፣ ጋቢና የተሰየመ ተሳፋሪ በእጅ ስልኩ መነጋገር ጀመረ። ‹‹ሰማህ በአንተ ቤት ሰው መርጠህ ልብህ ውልቅ ብሏል። እኔ እያለሁ እስኪ ምን ሌላ ጋ ያስኬድሃል? ‹ሥጋ ሞኝ ነው› አለ ያገሬ ሰው። ይኼው ለገንዘብ ብለህ የእጅህን አገኘህ አይደል…›› ይላል። ከጀርባው የተቀመጠ ጎልማሳ፣ ‹‹እውነት ነው፣ ሥጋ ሞኝ ነው። ታዲያ የበሬ ሳይሆን የሰው ሥጋ ነው ሞኝ…›› ይላል አጠገቡ ለተቀመጠች ቀዘባ። ወጣቷ፣ ‹‹መቼም ሰብቶ ከመታረድ የእኛ ሳይሻል አይቀርም…›› ስትለው መሀል መቀመጫ የተቀመጠች መነጽር ያደረገች ወይዘሮ ደግሞ፣ ‹‹ባለፈው በዓል ሰሞን በሬዲዮ ስለመላላጫና ስለፈረሰኛ ሲያወሩብን ሰነበቱ። አሁን ደግሞ እዚህ ስለሥጋ፡፡ ምናለበት ኑሮ ጣሪያ ነክቶብን በባዶ ወሬ ባታስፈስኩን?›› ስትል ትነጫነጫለች። ከጎኗ የተቀመጠ ቀበጥባጣ ወጣት፣ ‹‹አይገርምም? ዘንድሮ እኮ እኛነት ተረስቶ የእኔነት የሥጋ ወሬ ደመቀ…›› እያለ ንዴቷን ያባብሳል። ሥጋ ኪሎው ሁለት ሺሕ ብር ገብቶ የምን ተረብ ነው የተጀመረው ያስብላል፡፡ ሌላ ምን ይባላል! ‹‹እርግጠኛ ነኝ በዘንድሮ የሥጋ ዋጋ ምክንያት ‹ጥቂቶች መዥረጥ እያደረጉ ሲቆርጡ...
Bankers.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2025-02-06 09:15:12
በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ዘርፍ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ባንኮች በዘንድሮው የሒሳብ ዓማት አጋማሽ በአብዛኞቹ ቁልፍ የባንክ ሥራ መመዘኛዎች ዕድገት እያሳዩ መሆናቸው ተመላከተ። የአገሪቱ ባንኮችን የ2017 ግማሽ የሒሳብ ዓመት አፈጻጸም እንደሚያሳየው፣ በገበያ ውስጥ የሚገኙ 32 ባንኮች አጠቃላይ የሀብት መጠን ከአራት ትሪሊዮን ብር በላይ ነው፡፡  ባንኮች ከደረሱበት አጠቃላይ የሀብት መጠን ውስጥ ብልጫ ያለውን ድርሻ የያዘው መንግሥታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲሆን፣ የባንኩ አጠቃላይ የሀብት መጠን በ2017 ሒሳብ ዓመት አጋማሽ ላይ 1.97 ትሪሊዮን ብር መሆኑን ከመረጃው ለመረዳት ተችሏል። ቀሪው ደግሞ የግል ባንኮችና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ድርሻ ነው፡፡  በተቀማጭ ገንዘብ አሰባሰብ ረገድም የአገሪቱ ባንኮች የተቀማጭ ገንዘብ መጠን ከ23 በመቶ በላይ ዕድገት አሳይቷል፡፡ በሒሳብ ዓመቱ ግማሽ ላይ የሁሉም ባንኮች አጠቃላይ ተቀማጭ የገንዘብ (ከወለድ ነፃን ጨምሮ) ከ2.9 ትሪሊዮን ብር በላይ ደርሷል፡፡ ከዚህ ውስጥ በኢንዱስትሪው ከፍተኛውን የተቀማጭ ገንዘብ በማሰባሰብ ቀዳሚውን ድርሻ የያዘው መንግሥታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲሆን ከግል ባንኮች ደግሞ አዋሽ ባንክ በቀዳሚነት ተቀምጧል፡፡ በ2017 የሒሳብ ዓመት በግማሽ ዓመት አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘቡ መጠን 1.42 ትሪሊዮን ብር ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፣ ከዚህ...
Djibuti-1.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2025-02-05 22:10:38
ዓርብ ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም. የጂቡቲ ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ዘልቆ ገብቶ በአፋር ክልል ጥቃት አደረስ የሚለው ዜና ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኖ ነው የሰነበተው፡፡ የጂቡቲ መንግሥት ጥቃቱን ያደረሰው በድሮን መሆኑ መነገሩ፣ እንዲሁም በጥቃቱ በርካታ ሰላማዊ ዜጎች ተጎዱ መባሉ ጉዳዩ የበለጠ ትኩረት እንዲስብ አድርጎ ነበር፡፡ ዓርብ ዕለት ጂቡቲ በኢትዮጵያ ድንበር ጥቃት አደረሰች የሚለው ወሬ የተጎዱ ሰዎችን ከሚያሳዩና ለማየት ከሚያሰቅቁ ፎቶግራፎች ጋር ተያይዞ፣ በማኅበራዊ ገጾችና በተለያዩ የዜና አውታሮች መሠራጨቱ ትልቅ ትኩረት ቢስብም ነገር ግን ጥቃቱ ከዚያን ቀን ቀደም ብሎ ሐሙስ መካሄዱን ዘግይተው የወጡ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡ ያም ሆነ ይህ ግን በሁለት ወራት ለሁለተኛ ጊዜ የተፈጸመ ነው የተባለው ጥቃት ነፍሰ ጡርና ሕፃናትን ጨምሮ በትንሹ ለስምንት ሰዎች ሕልፈት ምክንያት መሆኑ ተነግሯል፡፡ የተለያዩ ፖለቲከኞችን ጨምሮ የአፋር ተወላጅ ማኅበራዊ አንቂዎችና ሌሎችም፣ ይህን የጥቃት ዜና አባሪ በማድረግ ኢትዮጵያ ድንበሯም ሆነ የአየር ክልሏ ተጥሶ ዜጎቿ በጎረቤት አገር መንግሥት የሚገደሉባት ሉዓላዊነቷን መጠበቅ ያቃታት አገር እየሆነች ነው የሚል መረጃ በሰፊው ማጋራት ቀጠሉ፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥትም ሆነ የአፋር ክልል መንግሥትና...
kibur-ministerrr.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2025-02-05 22:08:52
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia [ክቡር ሚኒስትሩ የሹፌራቸው ሁኔታ አላምር ብሏቸው ምን እንደሆነ እየጠየቁት ነው] ዛሬ አነዳድህ አላማረኝም። ምን አሉኝ ክቡር ሚኒስትር? አነዳድህ አላማረኝም! የሆንከው ነገር አለ? ጤንነት እየተሰማኝ አይደለም ክቡር ሚኒስትር። እስኪ ዳር ያዝና አቁመው። እሺ ክቡር ሚኒስትር …ይኸው። ምን ሆነሃል? ምን ያልሆንኩት አለ ብለው ነው ክቡር ሚኒስትር። እንዴት ምንድን የሆንከው። ግፊት አለብኝ። ስኳሬም ጨምሯል…. ኩላሊቴንም ይሰማኛል። መቼ ነው የጀመረህ? ከለውጡ ወዲህ ነው። እንዴ …ስድስት ዓመት ሙሉ ደብቀኸኝ እያስታመምክ ነው የቆየኸው? ኧረ እንደዚያ አይደለም ክቡር ሚኒስትር። እና መቼ ነው የጀመረህ? በዚህ ሳምንት ነው የጀመረኝ። ቅድም ከለውጡ ወዲህ ነው አላልክም እንዴ? አዎ፣ ብያለሁ።  ምንድ ነው የምታወራው? ክቡር ሚኒስትር ከለውጡ ወዲህ ነው የጀመረኝ እያልክዎት ነው። የትኛው ለውጥ? የውጭ ምንዛሪ ለውጥ። [ክቡር ሚኒስትሩ ከሕዝብ የቀረበ የግብር ቅሬታን በተመለከተ ከታክስ ጉዳዮች አማካሪያቸው ጋር እየተወያዩ ነው] ክቡር ሚኒስትር ማኅበረሰቡ ከፍተኛ ቅሬታ እያቀረበ ነው። ቅሬታ? አዎ ክቡር ሚኒስትር፡፡  ምን ሆንኩኝ ብሎ?  በቅርቡ ፀድቆ ተግባራዊ መሆን በጀመረው የተጨማሪ...
IMF.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2025-02-04 06:22:55
የዋጋ ንረትንና የብር አቅም መዳከምን ለመከላከል ጠንካራ የፖሊሲ ምላሽ ያስፈልጋል ብሏል በያሬድ ንጉሤ የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የኢትዮጵያ የዋጋ ንረት አኃዝ በተያዘው እ.ኤ.አ. 2025 አጋማሽ ድረስ 25 በመቶ እንደሚደርስ ተነበየ፡፡ አይኤምኤፍ ይህንን ያስታወቀው ኢትዮጵያን አስመልክቶ ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ሪፖርቱ ሲሆን፣ የዋጋ ንረቱ ወደ ነጠላ አኃዝ የሚወርደው ደግሞ እ.ኤ.አ. በ2028 እንደሆነ ገልጿል፡፡ ተቋሙ አክሎ እንደገለጸው የዋጋ ንረቱ ትንበያ የሚያሳየው ጭማሪ መንግሥት ተግባራዊ እያደረገ ያለው የነዳጅ ዋጋ ማሻቀብ የሚያስከትለው ነፀብራቅ ነው፡፡ እ.ኤ.አ. በ2025 የመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት ውስጥ የኢትዮጵያ መገበያያ ገንዘብ ወይም ብር ከውጭ አገሮች መገበያያዎች ጋር ሲነፃፀር ያለው አቅም  እንደሚቀንስም ነው አይኤምኤፍ በትንበያው የገለጸው፡፡ ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ በተለይ አገሮች የውጭ ምንዛሪ ገበያውን በፍላጎትና አቅርቦት ላይ የሚመሠረት (Floating Exchange Rate) ሲያደርጉ፣ በተደጋጋሚ የሚከሰትና የተለመደ እንደሆነ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በሐምሌ 2016 ዓ.ም. የውጭ ምንዛሪ ፖሊሲ ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ የአገሪቱ የዋጋ ንረት 19 በመቶ ከነበረበት ከመስከረም እስከ ጥቅምት 2017 ዓ.ም. ድረስ ወደ 17 በመቶ መውረዱን፣ የኢትዮጵያ...
Tigray.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2025-02-03 19:14:07
የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኃላፊዎች ስለጉዳዩ የተለያዩ ምላሾችን ሰጥተዋል ከዓለም አቀፍ አጋር አካላት በተገኘ 60 ሚሊዮን ዶላርና የፌዴራል መንግሥት ባቀረበው አንድ ቢሊዮን ብር ድጋፍ፣ የትግራይ ክልል የቀድሞ የፀጥታ ኃይሎችን ትጥቅ በማስፈታት ከሠራዊት የማሰናበትና መልሶ የማቋቋም (DDR) የመጀመሪያ ዙር ሥልጠና ከሦስት ሳምንታት በፊት መቋረጡ ተሰማ። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኅዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም. ያስጀመረው የሠራዊት ብተና (Demobilization)፣ ትጥቅ የማስፈታት (Disarmament) እና መልሶ ከማኅበረሰቡ ጋር የመቀላቀል (Reintegration) ፕሮግራም በመጀመሪያ ዙር በአራት ወራት ውስጥ 75,000 የቀድሞ የፀጥታ ኃይሎችን ለማሠልጠን ቢያቅድም፣ ዕቅዱ ግብ ሳይመታ ሰባት ሺሕ የቀድሞ የፀጥታ ኃይሎች የሥልጠናና መልሶ የማቋቋም ሥራ ከተከናወነ በኋላ መቋረጡን ከሪፖርተር ምንጮች መረዳት ተችሏል። የብሔራዊ ተሃድሶ የሥልጠናውን መጀመር አስመልክቶ በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. ማብራሪያ የሰጡት ኮሚሽነር አቶ ተመስገን ጥላሁን፣ ፕሮግራሙን በትግራይ ለማስጀመር በክልሉ ሦስት ቦታዎች በመቀሌ፣ በዕዳጋ ሐሙስና በዓድዋ በሚገኙ ማዕከላት የሚከናወኑ መሆናቸውን፣ በቅድሚያ በመቀሌ ማዕከል በመጀመር፣ በቅደም ተከተላቸው መሠረት ሥራውን የማስፋት ዕቅድ መያዙንና አስፈላጊ ከሆነም ሌሎች ሁለት ማዕከላት እንደሚጨመሩ መግለጻቸው ይታወሳል። በዚህም መሠረት ሥልጠናው በተጀመረበት ሁለት ቀናት ውስጥ 320...
Politics-44.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2025-02-03 19:12:56
‹‹ሕገ መንግሥቱ ወደፊት ይሻሻላል ብሎ ሕግ ማውጣት የሕግ አስተሳሰብ ሳይሆን የፖለቲካ አስተሳሰብ ነው›› የሕግ ምሁራን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ጥያቄ ተነስቶበት ከፍተኛ ክርክር የተደረገበት የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ በአብላጫ ድምፅ ፀደቀ፡፡ የፀደቀው የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ ምክር ቤቱ አጠቃላይ ትምህርትን በሕገ መንግሥቱ፣ አገሪቱ በፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች፣ እንዲሁም በቀረፀችው የትምህርት ሥልጠና ፖሊሲ መሠረት ለሁሉም ዜጎች በፍትሐዊነት ተደራሽ መሆኑን በማረጋገጥ፣ የትምህርት ጥራትን ያመጣል ተብሏል፡፡ ሐሙስ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም. በተካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባ አባላቱ ሕገ መንግሥቱን የሚቃረን ድንጋጌ መካተቱን በመጥቀስ፣ የምክር ቤት አባላት በረቂቁ ላይ ብርቱ ውይይትና ክርክር ካካሄዱ በኋላ፣ የተቃውሞ ድምፆች ቢሰሙም፣ አዋጅ ቁጥር 1368/2017 ሆኖ በአሥር ድምፀ ተዓቅቦ፣ በሁለት ተቃውሞና በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል፡፡ ረቂቅ ሕጉ ከወራት በፊት ከሚኒስትሮች ምክር ቤት ወደ ሕግ አውጪው ፓርላማ ሲመራ፣ በረቂቁ አንቀጽ 28 ላይ አንድ ተጨማሪ የአገር ውስጥ ቋንቋ ከፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች መካከል፣ የተማሪ ወይም የወላጅ ምርጫን ታሳቢ በማድረግ፣ በየደረጃው ባለው የትምህርት መዋቅር ተወስኖ እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ከሦስተኛ ክፍል ጀምሮ እስከ...
Chamber.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2025-02-03 07:34:43
ምርጫው የምክር ቤቱን ሕግና ደንብ ያላከበረ በመሆኑ እንደገና እንዲካሄድ ይጠየቃል ተብሏል ከሁለት ሳምንታት በፊት ጥር 11 ቀን 2017 ዓ.ም. 18ኛውን ጠቅላላ ጉባዔ በማድረግ ፕሬዚዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንትና የቦርድ አባላትን በመምረጥ፣ የሥልጣን ርክክብ ፈጽሞ የነበረው የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት፣ ድርጊቱን የፈጸመው፣ የማኅበራት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 341/1995 እና በ2004 ዓ.ም. የወጣውን መተዳደሪያ ደንብ ድንጋጌዎች የጣሰና ፍርድ ቤት ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም. የሰጠውን ትዕዛዝ የጣሰ በመሆኑ በትዕዛዙ መሠረት እንዲፈጽም ጥያቄ ቀረበ፡፡ የምክር ቤቱ የቦርድ አባል አቶ አበራ አበጋዝ እሸቴ በጠበቃቸው አማካይነት ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም.፣ ክስ መሥርተውባቸው ለነበሩት የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት፣ ለምክር ቤቱ ፕሬዚዳንት (በተደረገው 18ኛ ጠቅላላ ጉባዔ  ተቀይረዋል) ወ/ሮ መሰንበት ሸንቁጥና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ባቀረቡት ደብዳቤ፣ የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኢንቨስትመንት ምድብ ሦስተኛ ንግድ ችሎት ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም. የሰጠው ትዕዛዝ ተፈጻሚ እንዲሆን ጠይቀዋል፡፡ የጉዳዩ መነሻ አቶ አበራ አበጋዝ ከአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት አባልነታቸው መታገዳቸው ሲሆን፣...
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2025-02-03 07:31:36
በተሾመ ብርሃኑ ከማል  በአሜሪካ በ2018 ለንባብ ካበቁት አካዴሚያዊ መጻሕፍት ተጠቃሹ ‹‹ቋንቋና ነገድ በኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ሕዝብ ማንነትና ቅድመ ታሪክ›› የሚል ርዕስ ያለው የግርማ አውግቸው ደመቀ (ዶ/ር) መጽሐፍ ነው፡፡ ግርማ (ዶ/ር) የሥነ ልሳንና የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ባለሙያ ሲሆኑ፣ የምርምር ትኩረታቸው በአብዛኛው የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ታሪክና ሥነ መዋቅር ላይ ነው፡፡ በቅርቡ በእንግሊዝኛ ካሳተሟቸው መጽሐፎች መካከል የአማርኛ ጥንተ አመጣጥ፣ ሰዋስዋዊ ለውጥ በሴሜቲክ የአማርኛ ሰዋስው በዘመን ሒደት፣ የአርጎብኛ ንግግር ዓይነቶች ይገኙባቸዋል፡፡ ስለመጽሐፋቸው በመጽሐፉ የጀርባ ሽፋን እንደተገለጸው፣ መጽሐፉ ስለኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ቤተሰቦቻቸው የታሪካዊ ሥነልሳን ጥናት መውሰድ እስከሚችለው ጊዜ ገደብ ድረስ በመጓዝ መሠረታዊ መረጃ ያቀርባል፡፡ ቋንቋና ተናጋሪው የሚለያይ አይደለምና፣ ከቋንቋዎቹ አንፃር በመነሳት የኢትዮጵያን ሕዝብ ማንነትና ቅድመ ታሪክ ይዳስሳል፡፡ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ከተወሰኑ ብቸኛ ቋንቋዎች በስተቀር አፍሮ ኤሽያቲክና ናይሎ ሰሃራን ከሚባሉ ታላቅ ቤተሰቦች ይመደባሉ፡፡ ከጥቂት የናይሎ ሰሃራን ቋንቋዎች በስተቀር ሌሎቹ ለረዥም ጊዜ በኢትዮጵያ የነበሩ ናቸው፡፡ መጽሐፉ የአፍሮ ኤሽያቲክ ቋንቋዎች ከኤሽያ በተለያየ ወቅት ወደ ኢትዮጵያ ገቡ የሚለውን መላምት በስፋት መርምሮ ይህ ስለመሆኑ አሁን ያለው መረጃ ማረጋገጫ እንደሌለው ያሳያል፡፡ ከዚህም በላይ በኅብረተሰብ መካከል ስላለው...
Editoriakl.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2025-02-02 18:48:22
በዓለም ዙሪያ የሚካሄዱ ጦርነቶች በአብዛኛው እየቆሙ ወይም ወደ መጠናቀቂያቸው እየተቃረቡ ነው፡፡ እንደ ምሳሌ የሚጠቀሱትም በሩሲያና በዩክሬን፣ እንዲሁም እስራኤል ከሐማስና ከሂዝቦላህ ጋር ስታደርጋቸው የነበሩ ደም አፋሳሽ ጦርነቶች ወደ መጠናቀቂያቸው ተቃርበዋል፡፡ በተለይ በእስራኤልና በሐማስ መካከል የተኩስ አቁም ተደርጎ የእስረኞች ልውውጥ እየተደረገ ሲሆን፣ ከመኖሪያቸው ተፈናቅለው ተንከራታች የነበሩ ፍልስጤማውያን ስደተኞች ወደ ፍርስራሽነት የተለወጠችው ጋዛ በገፍ እየተመለሱ ነው፡፡ በእስራኤልና በሂዝቦላህ መካከል በተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ሊባኖሳውያን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ሰላማቸው እየተመለሰ ነው፡፡ ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካን ሥልጣነ መንበር ከተረከቡ ወዲህ ለዩክሬን የሚደረገው ድጋፍ በመቆሙ፣ ከሩሲያ ጋር የሚደረገው ጦርነት በእጅጉ እየተቀዛቀዘ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄዱ ደም አፋሳሽ ግጭቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ለሰላማዊ ንግግርና ድርድር ዕድል ይሰጥ፡፡ በኢትዮጵያ ልማት በስፋት ማከናወን የሚቻለው ሰላም ሲሰፍን ብቻ ነው፡፡ ሁለተኛ ጉባዔውን ለሦስት ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ እያካሄደ ያለው ገዥው ፓርቲ ብልፅግና በዛሬው ዕለት እንደሚያጠናቅቅ ይጠበቃል፡፡ በዚህ ጉባዔው ትልልቅ ውሳኔዎች እንደሚተላለፉ በፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንት ከቀናት በፊት በይፋ መነገሩ ይታወሳል፡፡ ከሚጠበቁት ትልልቅ ውሳኔዎች መካከል የሰላም ጉዳይ ግንባር ቀደም መሆን ይኖርበታል፡፡ አገሪቱን የመምራት ኃላፊነት የወሰደው...
plugins premium WordPress
Translate »