Etiópia

Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2025-11-09 20:54:58
(ክፍል አንድ) በታደሰ ሻንቆ ድሎች በአዝግሞት፣ በፈጣን ክንዋኔዎችና በዓድዋዊ ርብርብ እየተገኙ ወደፊት መራመድ የተከታተለበት ገራም አካሄድ ያለው አይደለም ታሪካችን፡፡ ብዙ ደፋ ቀናና ሄድ መለስ የሞላበት ነበር፡፡ በዚህ ሒደት ውስጥ ድል ማንጠባጠብና ማጎሳቆልም ታይቷል፡፡ የኢትዮ-ኤርትራ ፌዴሬሽን ፈርሶ ሙሉ ለሙሉ መቀላቀል መካሄዱና ያስከተላቸው ጣጣዎች አንድ የቅርብ ታሪክ ምሳሌ ነው፡፡ በለውጥ ፍላጎትና ትግል ውስጥ የምንፈጥረው ንቃተ ህሊናና ትልም የሚበጀንን የተቆናጠጠ መሆን አለመሆኑ ሌላ ፈተና ነው፡፡ ተራው ሰው ነጋ ጠባ የሚኖርበት ጉስቁልና እንዲቀልለት/እንዲወገድለት ከመፈለግ የዘለለ ቅዠት የለውም፡፡ ከዕውናዊ ችግሮች የዘለሉ ቅዠቶች በተለያየ ምክንያት የሚያደናብሩት ሊሂቃኑን ነው፡፡ በ1960ዎች ለለውጥ የታገሉ ወጣቶች የኢትዮጵያ ሕዝቦችን ከጉስቁልና የማላቀቅ ጠንካራ ፍላጎት የነበራቸውም ቢሆንም፣ የለውጥ ትልማቸው በኢትዮጵያ ተጨባጭ እውነታ ከመመራት ይልቅ፣ ዓለምን አነቃንቆ በነበረው ሶሻሊስት አስተሳሰብና በጊዜው በነበሩ የሃርነት ትግሎች አካሄድ የተሳበ ነበር፡፡ በዚህም ውስጥ ወጣትነታቸው፣ የትግል ልምዳቸው ትኩስነት፣ የኢትዮጵያን ዥንጉርጉር የሕዝቦች ሕይወት በደንብ የሰደረ የዕውቀት ስንቅ ጉድለት ሁሉ አስተዋጽኦ ሳያደርግ አልቀረም፡፡ ያ የሞቅ ሞቅ ትግልና የመሬት ሥሪት ለውጥ አፍላ ጊዜ ካለፈ በኋላ፣ በኢትዮጵያ ጠለቅ ባሉ ገጠሮች የነበረው የአኗኗርና የአስተሳሰብ...
Asteyayaet-5.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2025-11-09 20:53:14
ታማኝ ናቸው ከሚባሉት የቤት እንስሳት መካከል ውሾች ቀዳሚውን ሥፍራ ይይዛሉ፡፡ በመሆኑም ብዙ ሰዎች ቤታቸውንና ንብረታቸውን እንዲጠብቁላቸው ለውሾች አደራ ይሰጣሉ፡፡ ውሾችም የተሰጣቸውን ኃላፊነት በታማኝነት እንደሚወጡ ይነገራል፡፡ ውሾች ታማኝ ሆነው ከአሳዳጊያቸውና ከቤተሰብ አባላት አልፈው የጎረቤት ሁሉ ወዳጅ ቢሆኑም፣ በቤት ውስጥ አብረው የሚኖሩበት አጋጣሚ ለኢትዮጵያውያን እንደ ቅንጦት የሚታይ ነው፡፡ በከተማ ግቢ ውስጥ በተሠራላቸው ቤት አሊያም በረንዳ፣ በገጠር ሲሆን ደግሞ እንዲሁ ከዱር እንዲኖሩ የሚደረጉም ናቸው፡፡ በአንዳንድ ቦታም ውሾች ይሳደዳሉ፣ ይገደላሉ፡፡ ውሻን ማርባትና መንከባከብም እንደ ቅንጦት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ሆኖም ከዚሁ በተለየ ውሻን እንደ ቤተሰብ በመቁጠር አሠልጥነው፣ አስቤዛ መድበው፣ አሳክመውና አጥበው እንደ አጫዋችና ብቸኝነትን አስረሺ በመቁጠር ከሳሎናቸው የሚያስቀምጡም በርካቶች ናቸው፡፡ የውጭ ዝርያ ያላቸውና ድንክ ውሾች ደግሞ ከጠባቂነታቸው ባለፈም የቤት ጌጥ፣ የልጆችና የቤተሰብ አጫዋች ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ ለእንደዚህ ዓይነት ሰዎች ውሾችን መንከባከብ ከፍላጎት የመነጨና ሰብዓዊነት እንጂ ቅንጦት አይደለም፡፡ ውሻን ከመውደዳቸው የተነሳ በቤታቸው እንደሚሰበስቡ የነገሩን አቶ ጅብሪል ፈቃዱ፣ ውሾችን መንከባከብና መቀለብ ቅንጦት ነው የሚለውን ሐሳብ አይስማሙበትም፡፡ ከቤት እንስሳት ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳላቸውና እንደሚወዱ በመግለጽም፣ እንስሳትን መንካከብ ሰብዓዊነት እንደሆነ፣ እሳቸው...
Custom-Office.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2025-11-09 12:26:29
የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገበ ግብር ከፋይ የግብዓት ታክስ ተመላሽ የሚደረግለት ዓመታዊ ታክስ የሚከፈልበት አገልግሎት ወይም አቅርቦት ከአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ የካፒታል ዕቃዎች ግዥ ከፈጸመ ብቻ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ገቢዎች ሚኒስቴር የተሻሻለውን የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2016 ድንጋጌን መሠረት አድርጎ ያዘጋጀው የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመላሽ አፈጻጸም ረቂቅ መመርያ እንደሚያስረዳው፣ ወደፊት ሳይሸጋገር ተመላሽ የሚደረግ በብልጫ የተከፈለ የግብዓት ታክስን በሚመለከት ባሠፈረው አንቀጽ፣ የቫት ተመዝጋቢ የግብዓት ታክስ ተመላሽ የሚደረግለት ግብር ከፋይ በአንድ የሒሳብ ጊዜ ካከናወነው አቅርቦት ዋጋ 50 በመቶ ወይም ከዚያ በላይ የሚሆነው፣ ዜሮ የማስከፈያ ልክ ተፈጻሚ የሚደረግበት ከሆነ ነው ብሏል፡፡ የታክስ ተመዝጋቢው የተጨማሪ እሴት ታክስ ካስታወቀበት ጊዜ ጀምሮ በሚቆጠሩ ስድስት ወራት ጥያቄውን ካቀረበ፣ የታክስ ባለሥልጣኑ በሒሳብ ጊዜው በብልጫ የተከፈለውን የግብዓት ታክስ ተመላሽ ማድረግ እንደሚኖርበት ረቂቁ ደንግጓል፡፡ ሆኖም እነዚህ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ የሚሆኑት ዓመታዊ ታክስ የሚከፈልበት አቅርቦቱ ከአንድ መቶ ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ የቫት ተመዝጋቢ፣ ተቀናሽ የሚደረግ የካፒታል ዕቃዎች ግዥ ከፈጸመ መሆኑን ያስረዳል፡፡ በተጨማሪ ተቀናሽ ለሚደረገው የካፒታል ዕቃዎች ግዥ የግብዓት ታክስ ተቀናሽ የማግኘት መብት...
MOF.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2025-11-09 12:25:27
የገንዘብ ሚኒስቴር የንግድ ፈቃድ ካወጣበት ክልል ውጪ የንግድ ሥራ የሚያከናውን ነጋዴ፣ ግብሩን መክፈል ያለበት የንግድ ሥራውን በሚያከናውንበት ቦታ መሆን እንዳለበት አሳሰበ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ፣ ዋና ምዝገባና ፈቃዳቸው በአንድ ክልል ሆኖ፣ በሌላ ክልል በኮንስትራክሽንና በሌላም ዘርፍ የተሰማሩ ግብር ከፋዮች በሚያገኙት ገቢ ግብሩን መሰብሰብ የሚችለው የትኛው ክልል እንደሆነ ማብራሪያ እንዲሰጠው ለገንዘብ ሚኒስቴር በደብዳቤ በጠየቀው መሠረት፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ በዚህም በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 97፣ ክልሎች በአስተዳደራቸው ሥር ከሚገኙ ግብር ከፋዮች ላይ የንግድ ትርፍ ግብርና የሽያጭ ታክስ እንደሚጥሉና እንደሚሰበስቡ መደንገጉን የገለጸው ማብራሪያው፣ በሕግ ድንጋጌው መሠረት ታክስ የመጣልና የመሰብሰብ ሥልጣን የተሰጠው የንግድ ሥራው በሚከናወንበት ክልል እንጂ፣ የንግድ ሥራ ፈቃድ ለወጣበት ክልል እንዳልሆነ አስታውቋል፡፡ በመሆኑም አንድ ግብር ከፋይ በአንድ ክልል የንግድ ሥራ ፈቃድ አውጥቶ፣ በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ በተደነገገው መሠረት በተለያዩ ክልሎች በአጭር ምዝገባ የንግድ ሥራ የሚያከናውን ከሆነ፣ በእያንዳንዱ ክልል ለሚያከናውነው የንግድ ሥራ እንቅስቃሴ የተለየ የሒሳብ መዝገብ በመያዝ የገቢው ባለቤት ለሆነው ክልል ተገቢውን ግብር መክፈል እንደሚኖርበት ሚኒስቴሩ በሰጠው ማብራሪያ ገልጿል፡፡ አሠራሩ ታክስ...
Putin.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2025-11-07 00:30:35
የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የአሜሪካ የፖለቲካ ባህል ዝቅተኛ ደረጃ ላይ መገኘትን አስመልክተው ከሰጡት ሰሞነኛ ማብራሪያ የተወሰደ፡፡ ፕሬዚዳንት ፑቲን የተወሰኑ የአሜሪካ ተቋማትና ፖለቲከኞች የፖለቲካ ባህል ዝቅተኛ ደረጃ ላይ መገኘትን ሲያብራሩ፣ ኦስትሪያንና አውስትራሊያን የሚያምታቱ በመኖራቸው ምክንያት በቅጡ መነጋገር ማዳገቱንና ይህንን ምንም ማድረግ አይቻልም ነበር ያሉት፡፡ አሜሪካ ትልቅ አገር ናት ያሉት ፑቲን ሕዝቡም ትልቅ መሆኑን ተናግረው፣ ዝቅተኛ የፖለቲካ ባህል ያላቸው በርካታ ፖለቲከኞችን ሕዝቡ ችሎ መኖሩ በራሱ በእውነቱ ትልቅ ነገር ነው ሲሉም ተሳልቀዋል፡፡ የፕሬዚዳንት ፑቲንን አስገራሚ ንግግር ካዳመጡ የኤክስ (የቀድሞው ትዊተር) አስተያየት ሰጪዎች ብዙዎቹ፣ የአሜሪካ የወቅቱን የፖለቲካ ባህል ደረጃ በግልጽ የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ አንዳንዶቹ ንፅፅሩ የተጋነነ ነው ቢሉም፣ የአሜሪካ ፖለቲከኞች ጉዳይ ግን አሳሳቢ መሆኑን ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡ አንዲት አስተያየት ሰጪ ደግሞ፣ ‹‹የፑቲን አባባል ትክክል ነው፣ ሰርቢያንና ሳይቤሪያን እንደሚያምታቱት ማለት ነው…›› ብለዋል፡፡ Source link
Brief.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2025-11-06 16:12:29
የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት (አርኤስኤፍ) ኤል ፋሽርን መቆጣጠሩ የሱዳን መንግሥት መከላከያ የመጨረሻ ጠንካራ ይዞታን ከማሳጣት ባለፈም፣ አገሪቱን ወደ ሌላ የጨለማ ምዕራፍ መሸጋገሩን የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪ ድርጅቶች እየገለጹ ነው፡፡  ካለፈው ሳምንት ወዲህ በሱዳን የሰብአዊ መብት ጥሰትና ጥቃት እየተባባሰ መሆኑንም ያክላሉ፡፡ እ.ኤ.አ. በ2023 በሱዳን በተቀሰቀሰ የእርስ በርስ ጦርነት ከቀዬአቸው የተፈናቀሉ (ዩኤን ኤችሲአር) ባለፈው ሳምንት የዳርፉር ዋና ከተማ የሆነችውን ኤል ፋሽር የተቆጣጠረውና በመሐመድ ሃምዳን ደጋሎ (ሄሚቲ) የሚመራው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የአካባቢው ነዋሪችን ከቀያቸው በማፈናቀል ለአዲስ ጥቃት እየተዘጋጀ መሆኑ ደግሞ የሰብዓዊ ቀውሱን የከፋ ያደርገዋል ሲል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) አሳስቧል፡፡ ቀድሞም ለዓመታት በዘለቀ ግጭት ሳቢያ ለቸነፈር (ጠኔ) የተጋለጠው የዳርፉር ነዋሪ፣ አርኤስኤፍ በአል ፋሽር ያደረገውን ጭፍጨፋ በመፍራት መሰደድ የጀመረው ባለፈው ሳምንት ነበር፡፡ በተያዘው ሳምንት ደግሞ ሠራዊቱ ኤል ኦቢያድ ከተማን ለማጥቃት ማቀዱን ተከትሎ ነዋሪዎች ከኤል ኦቤያድ መውጣት ጀምረዋል፡፡ ሠራዊቱ አል ፈሽርን በተቆጣጠረ በሳምንት ጊዜ ውስጥ ከ70 ሺሕ በላይ ነዋሪዎች ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ የተፈናቃዮች ቁጥር እያየለ የመጣውም የሠራዊቱ ግድያና ሰብዓዊ መብት ጥሰት እየቀጠለ በመምጣቱ...
Exibition-3.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2025-11-06 16:11:20
በዶሮ፣ እንቁላል ወተትና ሥጋ ልማት ዘርፎች ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል የተባለው 14ኛው የኢትዮ የዶሮ ዕርባታና አሥረኛው የእንስሳት ኤክስፖና ዓውደ ርዕይ ከጥቅምት 20 እስከ ጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ የትረስት አግሮ ኮንሰልቲንግና ፋርሚንግ መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቡኑ አንዳርጌ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ በዶሮ ዕርባታ መስክ ኤክስፖ መዘጋጀቱ በዘርፉ ያሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እንዲተዋወቁ በማድረግ፣ የዕውቀት ሽግግር በመፍጠር፣ አዳዲስ ዝርያዎችን በማስተዋወቅና የገበያ ትስስር እንዲኖር በማድረግ በኩል የሚኖረው ጥቅም የጎላ ነው፡፡ በዶሮ ዕርባታ ዘርፍ የሚሰማሩ ግለሰቦች ቁጥር በየዓመቱ በመጨመር ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ ቀደም በዘርፉ ይታዩ የነበሩ የዕውቀትና የግንዛቤ ክፍተቶችም እየተሻሻሉና እየተቀረፉ ያሉ መሆናቸው ሲታይ ለዘርፉ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ያመላክታል ብለዋል፡፡ ‹‹በዶሮ ዕርባታ ዙሪያ የመኖ አቅርቦትና በሽታ ፈታኝ ችግሮች ናቸው›› የሚሉት አቡኑ (ዶ/ር)፣ በተለይ የመኖ ጥሬ ዕቃ ዋጋ ዕለት ከዕለት መጨመር ጋር ተያይዞ ለአርቢዎች ከፍተኛ ተግዳሮት መሆኑን፣ 90 በመቶ ለመኖ ግብዓት የሚያገለግሉት የአኩሪ አተርና የበቆሎ ምርት በመወደዳቸው ምክንያት የእንቁላል ዋጋ መጨመሩን ገልጸዋል፡፡ የዶሮ በሽታ በኢትዮጵያ ለሚገኙ የዶሮ አርቢዎች ትልቅ ሥጋት ፈጥሯል፡፡ ለበሽታው...
Biniyam.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2025-11-06 08:19:19
በኢትዮጵያ የኩላሊት ሕሙማን የሚገጥሟቸው ተግዳሮቶች በጣም ከባድና ውስብስብ ናቸው። በኩላሊት ሕክምና ላይ የሚታዩ ችግሮች የጤና አጠባበቅ ሥርዓቱን  የሚያንፀባርቁም ናቸው፡፡ በተለይ ዲያሊሲስና ንቅለ ተከላ ለሚፈልጉ ሕሙማን አገልግሎት ማግኘት  ፈታኝ ነው፡፡  መሆኑ ይነገራል። ሥር የሰደደ የኩላሊት መድከም  ያለባቸው ታካሚዎች በሳምንት ከሁለት እስከ ሦስት ጊዜ ዲያሊሲስ መውሰድ እንዳለባቸው ይመከራል፡፡ ይሁን ሕክምናው ውድ በመሆኑ፣ ይህም  ለአብዛኛው ታካሚ የሚቀመስ አይደለም። ለደም ግፊት፣ ለደም ማነስ፣ ለካልሲየምና ፎስፈረስ መቆጣጠሪያ የሚያስፈልጉ መድኃኒቶች በየጊዜው መወሰድ ያለባቸው ቢሆንም፣ ዋጋቸው ከፍተኛ በመሆኑ  ሕሙማን ብዙ ጊዜ ሕክምናቸውን ለማቋረጥ እየተገደዱ ሕይወታቸውን ያጣሉ። የመድኃኒት ዕጦትና ውድነት፣ በቂ የሕክምና አገልግሎት ተቋማትና የሕክምና መሣሪያ እጥረት ችግሮች ዛሬም ያልተፈቱ የኩላሊት ታማሚዎች ፈተናዎች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ማኅበር በኩላሊት ሕመም የሚሰቃዩ ወገኖችን ለመርዳት የተቋቋመ ማኅበር ነው፡፡ ማኅበሩን 11 የኩላሊት ታማሚዎች በጋራ የመሠረቱት ሲሆን፣ ከ200 በላይ አባላትን አፍርቷል፡፡ ለኩላሊት ታካሚዎች የመድኃኒት አቅርቦትና ሌሎች እገዛዎችን ከማድረግ አኳያ ምን እየሠራ ነው? የሚለውን የማኅበሩ ሰብሳቢን አቶ ቢኒያም አበራን አበበ ፍቅር አነጋግሯቸዋል፡፡ ሪፖርተር፡– የኢትዮጵያ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ማኅበር እንዴት ተመሠረተ? አቶ ቢንያም፡–...
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2025-11-06 08:18:10
በጌታነህ አማረ ለአንድ አገር ዕድገትም ሆነ ውድቀት ዋናውና ትልቁን ሚና የሚጫወተው የሚያራምደው ርዕዮተ ዓለም ወይም ዕሳቤ ነው፡፡ አሁን አሁን ዓለማችን ላይ ያሉ የርዕዮተ ዓለም ዕሳቤዎች ነባሮቹንና በየጊዜው የሚወለዱ ችግሮችን ተጋፍጠው መፍትሔ ለመስጠት አቅም ሲያንሳቸው በስፋት ይታያል፡፡ በመሆኑም እነዚህ ዕሳቤዎች ያለባቸውን ችግር መርምሮ ዕልባት መስጠት ፈጽሞ ለነገ የማይባል ትልቅ የቤት ሥራ ሊሆንና በተለየ መንገድ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ ይህንንም ተከትሎ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመጣው የመደመር ዕሳቤ ነባር ከሚባሉት ሊበራሊዝም፣ ሶሻሊዝም፣ ኮሙዩኒዝምና ኒዮ ሊበራሊዝም ለየት ባለ አተያይ የመጣ የዕሳቤ ዓይነት ነው፡፡ የእነዚህ ዕሳቤዎች አንዱ ከአንዱ ያላቸው ድክመትና ጥንካሬ የሚለካው ካላቸው የነፃነትና የእኩልነትን ችግር የመፍታት አቅም አንፃር ነው፡፡ እንግዲህ እዚህ ዓለም ውስጥ የችግሮች መነሻም ሆነ የመፍትሔዎች ምንጭ መሠረት ነፃነት ነው፡፡ ነፃነት ችግር ስላለበት ኢእኩልነትን የበኩር ልጁ አድርጎ ወልዶታል፡፡ በመካከላቸው ፀብ፣ አለመግባባትና ትልቅ ተቃርኖ አለ፡፡ የዚህ ውጤት ደግሞ በዓለም ላይ ትልቁ መስፈርት የሌለው መከራና ችግር እንዲኖር አድርጓል፡፡ እናም የዕሳቤዎች መወለድ ሁሉ ዋና ዓላማ በእኩልነትና በነፃነት መሀል ያለውን ተቃርኖ ወይም ልዩነት ከቻሉ ማጥፋት ወይም...
taxi.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2025-11-06 00:57:23
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia ፍርፋሪ! ከቀጨኔ ወደ አውቶቡስ ተራ ለመጓዝ የጠዋቱን ቅዝቃዜ ተቋቁመው የታክሲ ሠልፍ ላይ የተገኙ መንገደኞች ሰላምታ እየተሰጣጡ ይሳሳቃሉ፡፡ የጥንቷ ቀጨኔ በቅርብ ርቀት ከፒያሳና ከአዲሱ ገበያ ጋር ተጎራብታ ስትኖር ብዙዎቹ ነዋሪዎቿም ለበርካታ ዓመታት አንድ ላይ በመኖራቸው ትውውቃቸው የዝምድና ያህል ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ይመስላል የቀጨኔ ታክሲ ተራ ሠልፍ ላይ ሰላምታውና ሳቁ ደመቅ ያለው፡፡ የዛሬው ማለዳ ሳቅ ግን የሰሞኑን ግራና ቀኝ አጀንዳዎች የተንተራሰ ስለሆነ፣ ከሳቁ በስተጀርባ ያለው የኑሮ ክብደት በተረብና በስላቅ መታጀቡ አይደንቅም፡፡ ከጥንት ጀምሮ ከሸማ ሥራ እስከ ትራንስፖርት አገልግሎት፣ ከእህል ንግድ እስከ ሸቀጣ ሸቀጥና የተለያዩ ተግባራት የምትታወቀው ቀጨኔ ዛሬም ከኑሮ ጋር ከባድ ፍልሚያ የያዙ የልጅ ልጆች አፍርታለች፡፡ በዚህ ፍልሚያ ውስጥ ግን ሁሌም ሳቅና ተረብ ጠፍተው አያውቁም፡፡ ሳቁና ተረቡ ውስጥ ከአገር በቀል እስከ ዘመናዊ ዕውቀት የተላበሱ ዕድሜ ጠገብ ቁምነገሮችም አሉ፡፡ ጨዋነትና ትህትና ከስክነት ጋር ተዳምረው ሕይወትን ያለመልማሉ፡፡ የቀጨኔ ሕይወት ወትሮም እንዲህ ነው! የታክሲ ጥበቃ ሠልፉ ላይ የጦፈው ወሬና ሳቅ ደርቶ ሳለ ተረኛ ሚኒ...
Translate »