Etiópia

Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2024-07-27 00:55:55
በያሲን ባህሩ   የኦሮሚያ ብልፅግና      በአገር ደረጃ የብሔር ፖለቲካ በሥራ ላይ ከዋለበት ያለፉት ሦስት አሠርትና ተኩል ገደማ ዓመታት አንስቶ አገር የሚመሩ ሰዎችን በማንነታቸው እየመዘኑ መቃወምም ሆነ መደገፍ የተለመደ ተግባር ሆኗል፡፡ ምንም እንኳን ለይስሙላም ቢሆን የቡድን አመራር፣ ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነትና ድርጅታዊ አሠራር እንዳለና እንደነበረ ቢታወቅም የግለሰቦች ተፅዕኖ መኖሩም ሊፋቅ የማይችል ሀቅ ነው፡፡        አሁን ያለው የብልፅግና አመራርም ቢሆን በፓርቲው መሪና ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማንነት ብቻ ሳይሆን፣ ለሥርዓቱ ለመታመን ለሚለው ግምት እንዲመች በሚል በብዛት ወደ አመራርነት ከመጣው የሲቪልና ወታደራዊ አመራር መበራከት አንፃር የኦሮሞ ፖለቲከኞች (የኦሮሞ ሕዝብ አይደለም) ተፅዕኖ የጎላበት ነው ቢባል ግነት አይኖረውም የሚሉ በርካታ ናቸው፡፡      እንዳለመታደል ሆኖ ከኖረው የማንነት ተረክና ዕሳቤ አለመላቀቃችን እንጂ ዋናው መንግሥታዊ መለኪያና መመዘኛ መሆን ያለበት ግን፣ አገርን በእኩልነትና በፍትሐዊነት መምራት፣ ሰላምና ደኅንነትን ማረጋገጥ፣ ሙስናና ብልሹ አሠራርን ማስወገድ፣ የአገርን ሉዓላዊነትና ህልውና ማስጠበቅ፣ ልማትና ድህነት ቅነሳ ተግባራት ላይ መትጋት፣ ወዘተ መሆን ነበረበት፡፡ በእርግጥም መተማመንና ተጠያቂነት ያለው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መስፈን ቢጀምር፣ በቆዳ ስፋትም ሆነ በሕዝብ ብዛት ቀዳሚ የሆነውን ማኅበረሰብ የሚወክሉ...
Taxi.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2024-07-27 00:53:59
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia አሳርና ተስፋ! ከቱሉ ዲምቱ ወደ ቦሌ ጉዞ ልንጀምር ነው፡፡ ገና ከመንጋቱ ጎህ እንደ ቀደደ ረጅሙን ጉዞ በጊዜ ለመጀመር ሕዝብ አዳምና ሔዋን ተሠልፈዋል፡፡ የታክሲ ጥበቃ ሠልፉ ረዘም ስለሚል በዚያ የማለዳ ቅዝቃዜ እንደ አቅማቸው በደረቡዋቸው ሙቀት አመንጪ ልብሶች የተጀቦኑ ነፍሶች፣ ከጠቆረው ሰማይ ሥር ሆነው ዝናቡ ላያቸው ላይ እንዳይወርድ የሚማፀኑ ይመስላሉ፡፡ ታክሲ ጥበቃ ሠልፍ ላይ ሁሉም ዓይነት የኅብረተሰብ ክፍሎች ስለሚገኙ ወሬውም ሆነ ተረቡ እንደ ሰዎቹ አዋዋል ይለያያል፡፡ ከፊተኛው ሠልፍ አንድ እጇን በሌላኛው እጇ እያፋተገች በሰፊው ወግ የዘረጋች ቀጭን ጠይም ሴት፣ ‹‹እናንተ ዕድል የሚባል ነገር የለም የሚሉ ሰዎችን አትመኑ፡፡ በዚህ ምድር ልፋት 90 በመቶ ዕድል 10 በመቶ ስለሆኑ ነው ምስኪኖች ጠዋት በውርጭ ምሽት በቁር ታክሲ ጥበቃ መከራችንን የምናየው…›› ስትል፣ ‹‹እውነትሽን ነው እህቴ፣ ለምሳሌ እኔ ላለፉት 25 ዓመታት በቀን አሥራ ሁለት ሰዓት እየሠራሁ ምንም ጠብ ሳይልልኝ፣ ሁለት ዓመት ያልሠራ አንድ የማውቀው ጎረምሳ ይኸው ቪኤይት እየነዳ ጂፕላስ ሦስት ውስጥ ተንቀባሮ ይኖራል…›› እያለ አንዱ...
Melaku.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2024-07-26 15:47:52
በምትኩ የንግድ ተቋማት በአስገዳጅነት የንግድ ምክር ቤት አባል ይሆናሉ ተብሏል ግለሰብ ነጋዴዎች በአስገዳጅነት የንግድ ምክር ቤቶች አባል እንዲሆኑ የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አለመሳካቱና በምትኩ ኩባንያዎች በአስገዳጅነት አባል እንዲሆኑ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ስለመዘጋጀቱ ተጠቆመ፡፡  ከንግድ ምክር ቤቶች የማቋቋሚያ አዋጅ ጋር አከራካሪ ከነበሩ ጉዳዮች አንዱ አባልነት አስገዳጅ ይሁን አይሁን የሚለው ጉዳይ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ በሚገኘው ረቂቅ አዋጅ ግን የግለሰብ ነጋዴዎች የንግድ ምክር ቤት አባልነት በአስገዳጅነት ሳይሆን በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን መደንገጉ ታውቋል፡፡ ግለሰብ ነጋዴዎችን በአስገዳጅነት የንግድ ምክር ቤቶች አባል ማድረግ ሕገ መንግሥታዊ መብቶቻቸው ጋር የሚፃረር በመሆኑ ሐሳቡ ተቀባይነት ሳያገኝ መቅረቱ ተጠቁሟል፡፡ በዚህም ምክንያት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ በሚገኘው የንግድ ምክር ቤቶች አዋጅ ውስጥ ሊካተት እንዳልቻለ ሰሞኑን በተካሄደው የኢትዮጵያ ንግድ ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ተገልጿል፡፡ ባለፉት ስድስት ዓመታት የተለያዩ ማሻሻያዎች እየተደረጉበት በቆየው አዲሱ የንግድ ምክር ቤቶች ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ዝግጅት ላይ ተሳታፊ ሆነው የቆዩት የቀድሞ የኢትዮጵያ ንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት መላኩ እዘዘው (ኢንጂነር)፣ የአባልነት ጉዳይ አስገዳጅ ይሁን በሚል ብዙ ምክክር ሲረግበት...
በደቡብ-ኢትዮጵያ-ክልል-ጎፋ-ዞን-በመሬት-ናዳ-የሞቱ-ሰዎች-ቁጥር-ከ229-በላይ-ደረሰ-ሪፖርተር-Ethiopian-Reporter-1-Best-And-Reliable-News-Source-In-Ethiopia.png
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2024-07-26 15:46:31
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በደቡብ ኢትዮጵያ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬች ሻካ ጎዝዲ ቀበሌ ከእሑድ ሐምሌ 14 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት ጀምሮ በተከስት የመሬት መንሸራተት አደጋ ሕይወታቸውን ላጡና እስከ 500 ይደርሳሉ ለተበሉ ወገኖች ከነገ ከሐምሌ 20 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት ብሔራዊ የሐዘን ቀን ማወጁን ዛሬ ሐምሌ 19 ቀን 2016 ዓ.ም አስታወቀ፡፡ Source link
Politics-2.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2024-07-24 23:57:37
የሱዳን ጦርነት ከጀመረ አንድ ዓመት ከአራት ወራት አስቆጠረ፡፡ ጦርነቱ የ4.9 ሚሊዮኖች መኖሪያ የሆነችውን ዋና ከተማ ካርቱም ከተማን አውድሞ የዳርፉር፣ የአልጄዚራና የኮርዶፋን ግዛቶች ከተሞችንም አውድሟል፡፡ በሱዳን አሁን ወደ 10.5 ሚሊዮን ዜጎች ከቀዬአቸው ተፈናቅለዋል፡፡ ወደ ሁለት ሚሊዮን ዜጎች ደግሞ ወደ ጎረቤት አገሮች ተሰደዋል፡፡ ወደ ጎረቤት አገሮች ከተሰደዱት መካከልም ከ500 ሺሕ የሚበልጡት ወደ ቻድ ሲገቡ፣ ቀሪዎቹ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ስደተኞች ደግሞ ኢትዮጵያን ጨምሮ ወደ ሌሎች አገሮች ነው የተሰደዱት፡፡ ድንበር የለሽ የሐኪሞች ማኅበር ከትናንት በስቲያ ባወጣው ሪፖርቱ የሱዳን ቀውስን አሰቃቂ ብሎታል፡፡ ከአገሪቱ አጠቃላይ ሕዝብ ውስጥ 13 በመቶው ከቤት ንብረቱና ከቀዬው ለመፈናቀል የተገደደ ነው ይለዋል፡፡ በሱዳን የጦርነት ሰለባ የሆኑ ከ500 ሺሕ በላይ ሰዎችን እንዳከመ የሚናገረው ድርጅቱ፣ ከሦስት ሱዳናዊ አንዱ በጦርነቱ ለጉዳት ተጋላጭ መሆኑን በአሳሳቢነት ያስቀምጠዋል፡፡ በዳርፉር ግዛት ይህ ጦርነት የብሔር ግጭት ያስከተለ መሆኑን የሚጠቅሰው ድርጅቱ፣ በኤልጀኒና ከተማና በዙሪያዋ ከ10,000 እስከ 15,000 ሰዎች ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ተፈጽሞባቸዋል ይላል፡፡ በሱዳን ያለው ጦርነት አድማሱ የሰፋና አሰቃቂነቱ የጨመረ ቢሆንም፣ ነገር ግን ተፋላሚ ኃይሎች ግጭቱን የማቆም አንዳችም አዝማሚያ አይታይባቸውም፡፡ ባሳለፍነው...
IMG_20240724_182657_029.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2024-07-24 23:55:32
ኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን በረራ እንዲያሳድግ የሚጠይቅ ደብዳቤና ፈቃድ ከተሰጠው ከሁለት ሳምንት በኋላ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ ሙሉ በሙሉ መታገዱን የሚያሳውቅ ደብዳቤ እንዲደረሰው መደረጉ እንዳስገረመው ገለፀ። የኢትዮጵያ አየርመንገድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሐና አጥናፉ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ አየር መንገዱ ወደ ኤርትራ በረራ እንዳያደርግ መታገዱን የሚገልጽ ደብዳቤ እንዲደርሰው ከመደረጉ ከሁለት ሳምንት በፊት ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን በረራ እንዲያሳድግና የመጫን አቅማቸው ከፍተኛ የሆኑ አውሮፕላኖችን እንዲጠቀም ተጠይቆ ነበር። ” በረራ እንድናቆም የሚጠይቀው ደብባቤ ከመድረሱ ከሁለት ሳምንት በፊት የምናደርገውን በረራ ከ10 ወደ 15 እንድናሳድግ፣ የምንጠቀመውን መለስተኛ አውሮፕላን ወደ ከፍተኛ አውሮፕላን እንድናሳድግ ፣ በቀን ሁለት በረራ እንዲሁም በየሳምንቱ ዓርብ ሦስት በረራ እንድናደርግ ጠይቀውን ነበር” ሲሉ ሐና ተናግረዋል። አክለውም ፣ አየር መንገዱ በረራውን እንዳያሳድግ የሚጠይቅ ደብዳቤና ፈቃድ በተሰጠው በሁለት ሳምንት ውስጥ በረራውን እንዲያቆም የሚገልጽ ደብዳቤ ሲደርሰውና ይህም ባልተገባ መንገድ በማኅበራዊ ሚዲያ እንዲሰራጭ መደረጉ አስገራሚና አስደንጋጭ እንደሆነበት ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን በረራ እ.ኤ.አ. ከሴፕተምበር 30 ቀን 2024 ጀምሮ እንዲያቆም የሚያሳወቅ ደብዳቤ የደረሰው ቢሆንም፣ በረራውን እንዲያቆም...
kibur-ministerrr.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2024-07-24 13:37:56
ጤና ይስጥልኝ ክቡር ሚኒስትር? ሰላም! በአስቸኳይ እንደፈለጉኝ መልዕክት ደርሶኝ ነው የመጣሁት። አዎ። ይህንን ደብዳቤ እየውና በጠየቁት መሠረት እንዲፈጸምላቸው አድርግ። ጉዳዩ ምንድነው? ከአንድ ክልል የቀረበ የትብብርና ድጋፍ ጥያቄ ነው። የምን ትብብር ነው? ይህንን መጽሐፍ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱና በተጠሪ ተቋማት ለሚገኙ ሠራተኞች በመሸጥ ገቢውን እንድናስገባላቸው ነው የጠየቁት። ከደብዳቤው ጋር አያይዘውም ሁለት ሺሕ መጻሕፍቶችን ልከውልናል።  የምን መጽሐፍ ነው? የመደመር ትውልድ። ምን? ምነው ደነገጥክ? ይህ መጽሐፍ እኮ ለተቋማችን ተልኮ ነበር። አውቃለሁ።  እኮ …ሁሉም ሠራተኞች ገዝተውታል ማለቴ ነው።  ቢሆንም እንደሚሆን አድርገህ የተጠየቀውን ትብብር ፈጽምላቸው። ክቡር ሚኒስትር እኔ ሠራተኛውን ይህንን መጽሐፍ ድጋሚ ግዛ ማለት አልችልም። ለምን? እኔ እልችልም … ይከብደኛል እኮ ለምን? ለዚህ የትብብር ጥያቄ ማለት የምችለው አድን ነገር ብቻ ነው ክቡር ሚኒስትር። ምንድን ማለት ነው የምትችለው? አድርሰናል!  [ክቡር ሚኒስትሩ ከአማካሪያቸው ጋር ስለ ሰላም ድርድርና ሰላምን ስለማፅናት እየተወያዩ ነው] ክቡር ሚኒስትር ስለ ሦተኛው ዙር የሰላም ድርድር የሚያውቁት ነገር አለ? ሦስተኛ ዙር የሰላም ድርድር?  አዎ… የሚያውቁት ነገር የለም? ድርድሩ ተጠናቆ ፕሪቶሪያ ላይ ስምምነት ከተፈረመ ቆየ አይደል እንዴ?...
Untitled-Feb-2024-3.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2024-07-24 13:36:42
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ጉዳዩን እያጣራሁ ነው ብሏል በኤርትራ ትራንስፖርትና ኮሙዩውኒኬሽን ሚኒስቴር ሥር የሚገኘው የኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን፣ ከመስከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ አስመራ የሚደረጉ ማንኛውንም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎችን ማገዱን ገለጸ። ይህ የተገለጸው በባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በዛሬው ዕለት ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም. ለኅትመት በበቃው ‹‹ሓዳስ ኤርትራ›› የሚል ስያሜ ያለው ጋዜጣ ላይ ባወጣው ማስታወቂያ ላይ ነው። በሚኒስቴሩ በኩል ይፋ የተደረገው ማስታወቂያ እንደሚገልጸው፣ የአገሪቱ የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተፈጽመዋል ባላቸው ያልተገቡ የንግድ ተግባራትን ሲፈጽም ተገኝቷል በሚል ነው። ያልተገቡ የንግድ ተግባራት በሚል የተገለጹትም የተጓዦች የሻንጣ ስርቆት፣ ተልካሻ ሌብነት (Pilferage)፣ ጉዳት ማድረስ (Damage)፣ የተራዘሙ መዘግየቶችና ይህንን ተከትሎ የሚከሰቱ ምንም ዓይነት ካሳ ያልተከፈለባቸው ኪሳራዎች፣ ተገቢነት የሌላቸውና ፍትሐዊ ያልሆኑ የክፍያ ዋጋ ጭማሪዎች፣ እንዲሁም ሌሎች ያልተጠቀሱ ጉዳዩች እንዳሉበት በማስታወቂያው ተገልጿል። እነዚህ ‹‹ያልተገቡ የንግድ ተግባራት›› እንዲያርም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የተደረጉ ምልልሶች እስካሁን ድረስ ምንም ዓይነት ውጤት እንዳላስገኙም ገልጿል። የኤርትራው ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን በአየር መንገዱ የዕርምት ዕርምጃዎች ሊወሰዱ...
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2024-07-23 15:36:46
(የ3.2 ቢሊዮን ዓመታት በትግል የተገራ ጉዞ)    በሽብሩ ተድላ (ኢመረተስ ፕሮፌሰር) መግቢያ በአካባቢያችን ስለ ዝግመተ-ለውጥ (Evolution) ያለው ግንዛቤ ዝቅተኛ ስለሆነ፣ ይህ ጽሑፍ ያንን ግንዛቤ በተወሰነ መንገድ ለማዳበር፣ በተጉዳኝም ሳይንሳዌ ግንዛቤንና ሳይንሳዊ አስተሳሰብን ለማኸዘብ ያለመ ነው፡፡ በባህላችን ሰው ምን ይለኝ የሚል ሥጋት ስላለ ብዙ ሰዎች በጽሑፍ የመሳተፍ ፍላጎት የላቸውም፣ ይህ ተገቢ አይመስለኝም፡፡ ጠቃሚ የሆኑ የዕውቀት ማዳበሪያ መረጃዎችን ያሰባሰበ፣ ‹‹ሰው ምን ይለኝ ይሆን››? የሚለውን ያላነገበ፣ ጸሑፍ ማዘጋጀትና ለአንባቢያን ማቅረብ ጥቅም አለው ብዬ አምናለሁ፡፡ ይህም ጽሑፍ ያንን እምነቴን ያንፀባርቃል፡፡ ግንዛቤ ብሎም ዕውቀት፣ አስተያየት፣ አስተሳሰብ፣ እየጎለበተና እየጠራ ሊሄድ የሚችለው፣ ብሎም ተዓማኒነቱ የሚጎላና ተቀባይነት የሚኖረው፣ በውይይት፣ በክርክር ሲዳብር አንደሆነ ብዙ ግለሰቦች ይገነዘባሉ፡፡ በተጨማሪም በነፃነት ሐሳብን መግለጽ  የባህላችን አካል እንዲሆን ያስፈልጋል፣ ያንንም በይፋ መግለጥ ግድ ይላል፡፡ ይህንን በማጤን ለመማር ዕድል ያገኘን ግለሰቦች፣ ያገኘነውን ዕውቀት፣ እንዲሁም አስተሳሰብ ለአካባቢ ማኅበረሰብ ለማካፈል መጣር አለብን የሚል እምነት አለኝ፡፡ ለዝግመተ ለውጥ ዕውቀት የተገኘው በጣም ጥቂት ከሆኑ የአካል ቅሪቶችና የሕያው አካልን ቅርፅና ትግባር ወዘተ፣ ግንዛቤ ውስጥ አስገብቶ የመረጃ ምንጭ በማድረግ ነው፡፡ ሕያው...
koyita.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2024-07-23 15:34:07
አቶ ኡስማን ስሩር፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርናና የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ሻሸመኔ ከተማ ማደጋቸውንና መማራቸውን፣ በአግሮ ሜካኒክስ በዲፕሎማ በተመረቁበት ጂማ እርሻ ኮሌጅ ለሰባት ዓመታት ማስተማራቸውን፣ በትምህርቱ ጎን ለጎን እንደገፉበትም ይናገራሉ፡፡ ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ በዕፅዋት ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን እንደያዙ ይናገራሉ፡፡ ወደ ተወለዱበት ገጠር በመግባት ከባለሀብቶች ጋር የግብርና ልማት ሥራ መጀመራቸውን፣ በ1993 ዓ.ም. ጥር በስልጤ ዞን ላንፎሮ ወረዳ የግብርና ቢሮ ኃላፊ በመሆን ከግል ወደ መንግሥት ሥራ መቀላቀላቸውን ያስረዳሉ፡፡ የስልጤ ዞን ሲደራጅም የዞኑ ግብርናና ገጠር ልማት ኃላፊ ሆነው እንደተሾሙም ይናገራሉ፡፡ በስልጤ ዞን ለስምንት ዓመታት ቆይተው በ1998 ዓ.ም. ለሁለተኛ ዲግሪ ትምህርት ሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ መግባታቸውን ይጠቅሳሉ፡፡ ለመንግሥት ሥራ ትፈለጋለህ ተብለው የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ ተደርገው ለሁለት ዓመት ተኩል መሥራታቸውን፣ ወደ ታይላንድ ለሁለተኛ ዲግሪ ትምህርት ተልከው ዴቨሎፕመንታል ኮሙዩኒኬሽን መማራቸውን፣ ከዚያ መልስ በደቡብ ክልል ግብይትና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ማስተባበሪያ ቢሮ ለሁለት ዓመት መሥራታቸውን ይናገራሉ፡፡ ወደ ፌደራል ተዛውረው በፌደራል ኅብረት ሥራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር በመሆን አገልግለዋል፡፡ በ2013 በተደረገው...
plugins premium WordPress
Translate »