Etiópia

Abenezer.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-08 10:40:27
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደው ሰባተኛው አገራዊ ምርጫ ወጣቶችም የራሳቸውን ተሳትፎ ያደረጉበት ነው፡፡ ወጣቱ ትውልድ በምርጫው ወቅት ዝም ብሎ ተመልካች ከመሆን ይልቅ፣ ማን እንደሚመራውና ቀጣዩን ብሩህ ተስፋ ማን ሊያሳየው እንደሚችል አውጥቶና አውርዶ መምረጥ፣ ከፍ ሲል በመመረጥና ወጣቱን ክፍል ወደ ሥራ በማምጣት ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ተብሎ ይታመናል፡፡ ይሁን እንጂ ለአገሪቱ ዕጣ ፈንታ፣ ለሰላምና መረጋጋት መፍትሔ ይሆናል ያለውን መንግሥት ለመምረጥ ወይም ለመመረጥ በስፋት ከፊት ወጥቶ ሲሳተፍ አልተስተዋለም፡፡ፖለቲካዊ ምኅዳሩን በመጠራጠር ራሳቸውን ከምርጫ ሒደት ያቀቡ፣ ከፍ ሲል ምርጫ መኖር አለመኖሩን የማያውቁ ወጣቶች አልጠፉም። ሆኖም በምርጫ የተሳተፉም ሆኑ ያልተሳተፉ ወጣች ከምርጫ ማግሥት ከሚመረጠው መንግሥት በርካታ ነገሮችን መጠበቃቸው አይቀርም፡፡ በአሁኑ ወቅት በርካታ ወጣቶች በኢኮኖሚ ቀውስ፣ በኑሮ ውድነትና በሥራ አጥነት ችግር ውስጥ በመሆናቸው የሚመረጠው መንግሥት የወጣቱን ጉልበት ለሥራ ማዋል እንዳለበት ይታመናል። ሥራ አጥነትና ተስፋ መቁረጥ በአንዳንድ አካባቢዎች ዘረፋን፣ ቅሚያንና ማኅበራዊ ቀውሶችን እያስፋፋ ከመሆኑም በላይ በርካታ ወጣቶችን ለስደትና ለተለያዩ ሱሶች እየዳረገ ይገኛል። ስለዚህ የሚመሠረተው መንግሥት ወጣቱን ከሥራ አጥነት ማላቀቅ፣ የሚታዩትን ማኅበራዊ ስብራቶች መጠገንና ሁለንተናዊ የፖለቲካና...
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-08 10:39:15
በተሾመ ብርሃኑ ከማል ልዩ ልዩ ስታቲስቲካዊ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት አብዛኛው የዓለም ሕዝብ ወጣት ነው፡፡ በዓለም ላይ እጅግ አስገራሚና አስደናቂ ሥራዎች የተከናወኑትም በአብዛኛው በወጣትነት ዕድሜ ነው፡፡ ስለሆነም አገራችንን ጨምሮ በሌሎች አገሮች ያሉና የነበሩ ወጣቶች ሕዝብ አስተባብረው አገራቸውንና ዓለማቸውን መርተዋል፡፡ በርካታ አሳሾች በመላው ዓለም የተንቀሳቀሱት በወጣትነት ዕድሜያቸው ነው፡፡ ብዙ ነገሮች የተፈጠሩት በወጣትነት ዕድሜ ነው፡፡ የዓለማችን የሃይማኖት መሪዎች እምነታቸውን፣ አመለካከታቸውንና ፍልስፍናቸውን ይዘው ብቅ ያሉት በወጣትነት ዕድሜያቸው ነው፡፡ ጥንትም ሆነ ዛሬ ዓለም የወጣቶች ናት፡፡ በዓለማችን፣ በክፍለ አኅጉራችን፣ በአገራችን ብሎም በክልላችን የሚገኙ ወጣቶች በአፍላ የጉርምስና ጊዜያቸው አንዳች ተግባር አከናውነው ለመታወቅ ይመኛሉ፡፡ ለምሳሌ በአንድ አነስተኛ የገጠር ቀበሌ የሚገኝ ወጣት አንድም በአካባቢው እንዳለ ሀብታም ገበሬ፣ ጀግና ነጭ ለባሽ፣ ወታደር፣ አስተማሪ፣ የሃይማኖት መሪ ወይም ሌላ ለመሆን ይመኛል፡፡ በዞንና በክልል ከተሞች የሚገኝ ወጣት ደግሞ በአካባቢው ከሚያየው፣ በሬዲዮ ከሚሰማው፣ በቴሌቪዥን ከሚመለከተውና በትምህርት ቤት አስተማሪው ከሚነግሩት ትልቅ ሰው መካከል ከእሱ ዝንባሌ ጋር የሚሄደውን አንዱን ወይም ሁለት፣ ሦስቱን በመምረጥና እንደ አርዓያ በመውሰድ ‹‹እኔም እንደ እሱ/እንደ እሷ እሆናለሁ፤›› ብለው ይመኛሉ፡፡ በመሠረቱ በየትኛውም አኅጉርና አገሮች...
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-08 04:03:47
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት በሚገኘው የካርቦን ገበያ ረቂቅ አዋጅ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚከናወን ማንኛውንም የካርቦን ልቀት ቅነሳ በብሔራዊ ደረጃ በሚቋቋም ባለሥልጣን መጽደቅ እንዳለበት የሚያስገድድ የሕግ ድንጋጌ አካቷል፡፡ የኢትዮጵያ የካርቦን ገበያ ረቂቅ አዋጅ ማንኛውም የካርቦን ልቀት የቅነሳ ተግባር በኢትዮጵያ ውስጥ ሕጋዊ ወይም የፀና ሆኖ የካርቦን ክሬዲቶችን ጨምሮ ማናቸውም የቅነሳ ውጤት የሚያስገኘው በተሰየመው የብሔራዊ ባለሥልጣን የፀደቀ ከሆነ ብቻ ነው ሲል ይደነግጋል፡፡  ማንኛውም ሰው በዚህ አዋጅ መሠረት በቀጣይ በሚሰየመው ብሔራዊ ባለሥልጣን በመመዝገብ፣ የተቃውሞ አለመኖሩን የሚያረጋግጥ ደብዳቤ እንዲሁም የቅነሳ ተግባር የማፅደቅ ደብዳቤ ሳያገኝ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የካርቦን ልቀት የቅነሳ ተግባር ማከናወንን ይከለክላል፡፡ በሚቋቋመው ብሔራዊ ባለሥልጣን የፀደቀ የቅነሳ ተግባር በኢትዮጵያ የካርቦን መዝገብ ውስጥ ተመዝግቦ፣ በኢትዮጵያ የካርቦን መዝገብ ማረጋገጫ ደብዳቤ የተሰጠው አካል በተሰጠው በስድስት ወራት ውስጥ የካርን ቅነሳውን በተጨባጭ በተግባር መጀመር እንዳለበት በረቂቁ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚከናወን የቅንሳ ተግባር የሚመነጩ የካርቦን ክሬዲቶችን ጨምሮ የቅነሳ ውጤቶች ባለቤቱ የኢትዮጵያ መንግሥት ስለመሆኑ የሚደነግገው ረቂቁ፣ በፓሪስ ስምምነት መርሆችና ዳግም ቆጠራን ማስቀረት፣ አካባቢያዊ ደኅንነት፣ አካታችነት፣ የአካባቢያዊና የማኅበራዊ ጥበቃ ሥርዓቶች፣ ፍትሐዊና...
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-07 14:33:45
አገር አቀፍ የስታትስቲክስ ጥናት ለማካሄድ ከተቋሙ ፈቃድ ማግኘት ያስፈልጋል የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ ሥርዓትን በበላይነት የሚመራ የብሔራዊ ስታትስቲክስ ቦርድ የሚያቋቁም ረቂቅ ሕግ ለፓርላማ ቀረበ፡፡ ረቂቁ የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በይፋ ስታትስቲክስ የማመንጨትና የማሠራጨት ኃላፊነት የተጣለበት፣ ራሱን የቻለ፣ ሙያዊ ነፃነት እንዲኖረው ተደርጎ እንዲቋቋም የሚያደርግ ነው፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ጉባዔ የስታትስቲክስ አገልግሎት ነፃ ሆኖ እንዲቋቋም የሚፈቅድ ረቂቅ ላይ ተወያይቷል፡፡ የሚቋቋመው ቦርድ ተጠያቂነትን በማረጋገጥ የስታትስቲክስ ሥራዎችን በአገር ቅድሚያ ከሚሰጣቸው የልማት አጀንዳዎች ጋር መጣጣሙን እንደሚያረጋግጥ፣ በሴክተር መሥሪያ ቤቶች መካከል በዘላቂነት መኖር ያለበትን ትብብር ያጠናክራል ይላል ረቂቅ ሕጉ፡፡ የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ይፋዊ ስታስቲክስን የማመንጨትና የማሠራጨት ኃላፊነት የተጣለበት ራሱን የቻለ ሙያው ነፃነት ያለው ተቋም ሆኖ ዕውቅና እንዲኖረው ተገልጾ፣ ተጠሪነቱ ለፕላንና ልማት ሚኒስቴር መሆኑ ተደንግጓል፡፡ ለምክር ቤቱ ፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር ዕይታ የተመራው ረቂቅ፣ ዘጠኝ አባላት ያሉት ብሔራዊ የስታትስቲክስ ቦርድ እንደሚቋቋም ይጠይቃል፡፡ የቦርድ አባላቱ የመንግሥት አካላት፣ የአካዴሚክና የምርምር ተቋማት፣ የግል ዘርፍ ተወካዮች፣ የሙያ ማኅበራት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና ታዋቂ...
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-07 14:32:40
ታካሚዎች በታዘዘላቸው መመርያ መሠረት መድኃኒት በአግባቡ አለመጠቀማቸው፣ ለሱስ የመጋለጥ ሥጋት ማሳየታቸው ወይም የሕክምና ውጤታማነት ማጣት እንደገጠማቸው ሲታወቅ፣ የመድኃኒት ባለሙያዎች መድኃኒቱን በድጋሚ ከመስጠት ተቆጥበው ታካሚውን ወደ ታከመበት ሐኪም ቤት እንዲልኩ የሚያስገድድ መመርያ በሥራ ላይ ዋለ፡፡   ይህ አሠራር መድኃኒትን ያለአግባብ ከመውሰድና በሱስ ከመጠመድ የሚመጡ ማኅበራዊና አካላዊ ጉዳቶችን ለመግታት ወሳኝ ሚና ይጫወታል ተብሏል። በኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሔራን ገርባ በተያዘው ግንቦት ወር ፀድቆ በሥራ ላይ የዋለው ‹‹አግባባዊ የመድኃኒት አጠቃቀም መመርያ ቁጥር 1138/2018›› ከሰባት ዓመታት በፊት በተመሳሳይ ስም ፀድቆ እስካሁን ፀንቶ የቆየው መመርያ ላይ ማሻሻያዎች ያደረገ ሲሆን አዳዲስ ድንጋጌዎችንም አካቷል። ከተካተቱት አዳዲስ ድንጋጌዎች መካከል ኤሌክትሮኒክስ የመድኃኒት ማዘዣ ስለመጠቀም፣ የፀረ ተዋህሲያን መድኃኒቶችን በተዋህሲያን መላመድን መከላከልና መቆጣጠር፣ እንዲሁም መድኃኒትን በድጋሚ ስለማደል የተመለከቱት አንቀጾች ይገኙበታል። በአንቀጽ 12 መድኃኒትን በድጋሚ ስለማደል በሠፈሩት ድንጋጌዎች መሠረት፣ ማንኛውም የመድኃኒት ባለሙያ መድኃኒት በአንድ ማዘዣ እንደገና ለማደል የሚችለው የሕክምና ባለሙያ በመድኃኒት ማዘዣው ላይ በድጋሚ ማደል እንደሚቻል የገለጸ እንደሆነ ብቻ መሆኑን፣ እንዲሁም ማንኛውም የመድኃኒት ባለሙያ መድኃኒት በድጋሚ ሲያድል በመድኃኒት ማዛዣው ላይ...
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-07 07:50:57
ለፓርላማው በቀረበው የምግብ ሥርዓትና ሥርዓተ ምግብ ምክር ቤትን በሚያቋቁመው ረቂቅ አዋጅ፣ የመቀንጨር ችግር አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተመላከተ፡፡ ከመቀንጨርና ከሥርዓተ ምግብ መዛባት ጋር የተያያዙ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች መጠን መጨመር በጤና፣ በትምህርት፣ በአካባቢያዊ፣ በምርታማነትና በማኅበራዊ መስተጋብር፣ እንዲሁም በአገር ኢኮኖሚ ላይ እያሳደረ ያለውን አሳሳቢ ችግር ለመቀነስና ለማጥፋት ያግዛል የተባለ ረቂቅ ሕግ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣ የምግብ ሥርዓትና ሥርዓተ ምግብ ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ለዝርዝር ዕይታ ለጤና ማኅበራዊና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ለምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጠሪ የሆነ  የምግብ ሥርዓትና ሥርዓተ ምግብ ምክር ቤት ያቋቁማል፡፡ ምክር ቤቱ የምግብ ሥርዓትና ሥርዓተ ምግብን በተመለከተ ከፈጻሚ ተቋማት የሚቀርብለትን አፈጻጸም በመገምገም አቅጣጫ የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የመቀንጨር ችግር አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የሚያስረዳው ረቂቁ፣ ሁኔታው በዚሁ ከቀጠለ፣ ዜጎች ለልዩ ልዩ የጤና ችግሮች ለሞት፣ ለፈጠራ ችሎታና ለትምህርት አቀባበል ውስንነት እንደሚዳርግ ተብራርቷል፡፡ በ2018 ዓ.ም. ይፋ በተደረገው የጤና ሥነ ሕዝብ ዳሰሳ ጥናት መሠረት፣ በኢትዮጵያ 40 በመቶ ወይም...
Real-Estate.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-07 07:49:32
የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ተብለው የሚቋቋሙ ፈንዶች ከዓመት ትርፋቸው ቢያንስ ዘጠና በመቶውን ለሰነደ ሙዓለ ንዋይ ባለቤቶች በትርፍ ድርሻ መልክ እንዲያከፋፍሉ፣ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ረቂቅ መመርያ አዘጋጀ፡፡  ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ይፋ የተደረገው ረቂቅ መመርያ፣ በካፒታል ገበያ አዳዲስ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለማስፋፋትና ባለሀብቶችን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። ባለሥልጣኑ ቁጠባን ወደ ኢንቨስትመንት ለማምራትና የፋይናንስ አካታችነትን ለማስፋት በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 ያዘጋጀው ‹‹የጋራ ኢንቨስትመንት ፈንድ ረቂቅ መመርያ›› እንደሚያሳየው፣ የጋራ ኢንቨስትመንት ፈንድ ማለት፣ ከበርካታ ባለሀብቶች የተሰበሰበ ገንዘብ በአንድ ላይ በመመደብ በባለሙያዎች የሚተዳደርና የአክሲዮኖች፣ የቦንዶች ወይም ሌሎች የፋይናንስ ሰነዶች ውህድ በመፍጠር ከትርፍ ተጠቃሚ የሚያደርግ የኢንቨስትመንት ሥልት ነው። በዚህም ለሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ፈንድ ለመመዝገብ ከሚያበቁ መሥፈርቶች አንዱ፣ ከፈንዱ የተጣራ የሀብት ዋጋ ቢያንስ 80 በመቶ ገቢ የሚያስገኝ ሪል ስቴት ላይ ኢንቨስት ማድረግ የሚል መሆኑ በረቂቁ ተደንግጓል። ለእያንዳንዱ የሒሳብ ዓመት ሊከፋፈል ከሚችለው ትርፍ ወይም ገቢ ቢያንስ 90 በመቶ የሚሆነውን ደግሞ፣ ለሰነደ ሙዓለ ንዋይ ባለቤቶቹ በትርፍ ድርሻ መልክ ማከፋፈል እንደሚኖርበት ያስገድዳል። ገቢ የሚያስገኝ ሪል ስቴት...
Since-Acdamay.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-07 00:50:15
በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ አገር በቀል ዕውቀቶችን ለመመዝገብ 47 ዩኒቨርሲቲዎች የጀመሩት ሒደት 90 በመቶ መጠናቀቁ ተገለጸ፡፡ ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዴሚ በቋንቋ፣ በጤና፣ በግብርናና በእንስሳት እንክብካቤ ዘርፍ ትኩረቱን ያደረገ ‹‹አገር በቀል የዕውቀት ሥርዓት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ልማት›› በሚል ርዕስ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደ የውይይት መድረክ ነው፡፡ ውይይቱን የመሩትና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ የኅብረተሰብ ጤና ሳይንስ ተመራማሪ መንገሻ አድማሱ (ፕሮፌሰር)፣ የአገር በቀል ዕውቀቶች ምዝገባው 90 በመቶ መጠናቀቁንና በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ሙሉ በሙሉ እንደሚያልቅ ተናግረዋ፡፡ በመጀመሪያው ዙር በ47 ዩኒቨርሲቲዎች ስምንት ዘርፎች ተለይተው ምዝገባው እየተከናወነ መሆኑንና እነዚህም ጤና፣ የሰላም ግንባታና የግጭት አፈታት፣ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም፣ የመንግሥት አስተዳደር፣ የአየር ንብረት፣ የልጆች አስተዳደግ፣ የቀን አቆጣጠርና ግብር መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ ሰነድነት የመቀየሩ ሥራ ረዥም ሒደት የሚጠይቅ እንደሆነ፣ ትንታኔውን እንዴት ማከናወን እንደሚቻል ሥልጠና እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡ ሥራውን በዋናነት ኃላፊነት ወስዶ እያከናወነ የሚገኘው የትምህርት ሚኒስቴር መሆኑን ያስታወሱት መንገሻ (ፕሮፌሰር)፣ ይህንን ከግምት ውስጥ በማስገባት የአገር በቀል ዕውቀት ምዝገባ ሲጠናቀቅ፣ የትምህርት ሥርዓት በማድረግ በካሪኩለም መልክ ይዘጋጃል የሚል የተሳሳተ ግምት...
Picture-2.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-07 00:48:50
ቀጣይነት ያለው የውጭ ምንዛሪ የአቅርቦት ሥርዓት መፍጠር እንደሚገባ ተመላክቷል በቅርቡ ይፋ የተደረገው አዲሱ የንግድ ፖሊሲ የገቢ ንግድ ታሪፎችን በማንሳት ኢትዮጵያ በአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ውስጥ፣ ከአገሮች ጋር የምታደርገውን የንግድ ልውውጥ ያቀላጥፋል ተባለ፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከቀናት በፊት ያፀደቀው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የንግድ ፖሊሲ፣ የኢትዮጵያ የንግድ ሥርዓት የሚመራ፣ ምርታማነትን ለማሳደግና የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት የሚያገለግል ዋነኛ መሣሪያ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ውስጥ ከአገሮቹ ጋር ያላትን የንግድ ልውውጥ ለማቀላጠፍ፣ የንግድ ፖሊሲው ዓይነተኛ መፍትሔ እንደሚሆን በፖሊሲ ሰነዱ ሠፍሯል። ለዚህም የገቢ ንግድ ታሪፎችን በማንሳት ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ እንደሚያስችል የወጣው ሰነድ ያሳያል፡፡ የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና በአገሮች መካከል የኢኮኖሚ ትስስርን ለማመቻቸት የተነደፈ በመሆኑ፣ ከአገር ውስጥ ኩባንያዎች ጋር ግንኙነት ለሚፈጥሩ የውጭ ኩባንያዎች የተለያዩ ማበረታቻዎችን መስጠት የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ፖሊሲው እንደሚረዳ ተጠቁሟል። አገራዊ ተወዳዳሪነትን የማሳደግ፣ የወጪ ንግድ ዕድሎችን የማስፋፋትና የወጪ ምርቶችን በዓይነት፣ በመጠንና በመዳረሻ ገበያ የማስፋት፣ ፈጠራን የማበረታታት፣ እንዲሁም በአገር ውስጥ፣ በጠረፍ ንግድና በመዳረሻ ገበያዎች ያሉትን መሰናክሎችን ለመቅረፍ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት የሚያስችል እንደሚሆን ሰነዱ...
Politics-5.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-06 18:42:34
ደረሰ የተባለው ጥቃት ከፍተኛ የሕዝብ ቁጣ ቀስቅሷል መንግሥት የማያዳግም ዕርምጃ እየወሰደ መሆኑን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል መንግሥት በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ፣ ዋቤና ሙኔሳ ወረዳዎች ውስጥ በኦርቶዶክስ ምዕመናን ላይ የሚደርሱ ተደጋጋሚ ጥቃቶችን እንዲያስቆም ተጠየቀ፡፡ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚገኘው የአርሲ አገረ ስብከት ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት፣ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. የደረሰውን ሞትና የንብረት ውድመት ለማሳወቅ በተጻፈው ደብዳቤ ነው ጥያቄው የቀረበው፡፡ አገረ ስብከቱ ከዚህ ቀደም በቤተ ክርሲያንና በምዕመናን ላይ በተደጋጋሚ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለማስቆም፣ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ደረጃ ከከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ውይይት ተደርጎ በዘላቂነት መፍትሔ እንዲያገኝ መሞከሩን፣ ነገር ግን አሁንም ጥቃቶቹ መቀጠላቸውን ገልጿል፡፡ በሰረካ ወረዳ ለ101 ዓመታት የቆየውና የአገር ቅርስ የሆነው የተለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ተቃጥሎ መውደሙን፣ በአጥቢያው ነዋሪ የሆኑ ዘጠኝ ምዕመናን በአሰቃቂ ሁኔታ በታጣቂዎች ሕይወታቸው ማለፉን አገረ ስብከቱ በደብዳቤው አስታውቋል፡፡ ​በሰረካ ወረዳ በጠለታ፣ ካራ ኩፍቴ፣ ዘዲቡ እሬቻ፣ ቅዱስ ሚካኤል፣ ሱንቴ ቅድስት ማርያም፣ በቦንግዶ አቦ፣ ሌንጫ ኦዳ፣ በጂንሶና...
Translate »