Etiópia

Screenshot_20260423_135238_Video-Player.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-24 02:20:01
በአትሌትና ኢንተርፕረነር ኃይሌ ገብረስላሴ ባለቤትነት የሚመራው፣ የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ግሩፕ፣  በደብረብርሃን ከተማ በ1.9 ቢሊዮን ብር ያስገነባውን 11ኛውን ሪዞርት ዛሬ ሚያዚያ14 ቀን2018 ዓም አስመረቀ። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሃን ከተማ የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደርና ሌሎች ሀላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተመርቆ ወደ ስራ ገብቷል። በ8000 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው  ሪዞርቱ፣ 123  የመኝታ ክፍሎች የያዘ ሲሆን ለከተማዋ ወጣቶች የስራ እድሎችን እንደሚፈጥር ሻለቃ ኃይሌ   በምርቃቱ ወቅት ተናግረዋል።  ​ይህ ግዙፍ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት በኢንዱስትሪ ከተማዋ ደብረ ብርሃን ያለውን ከፍተኛ የእንግዳ ማረፊያ ፍላጎት ለመሙላትና የቱሪዝም ዘርፉን ለማነቃቃት ከፍተኛ  ሚና እንደሚጫወትም  ገልፀዋል ።  ሆቴሉ በህንፃ ጥራቱና በውስጡ በያዛቸው ዘመናዊ መገልገያዎች በከተማዋ ቀዳሚ  እንደሚሆን የገለጹት ሻለቃ ሀይሌ፣   አራት የተለያዩ ሬስቶራንቶች፣ የመጠጥ አገልግሎት የሚሰጡ ባሮች፣ ጂምና የሳውና አገልግሎቶችን ያካተተ እንዲሁም  ትላልቅ ስብሰባዎችንና ማህበራዊ ሁነቶችን ለማስተናገድ የሚያስችሉ ስድስት ዘመናዊ አዳራሾችንም  ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል። ግሩፑ ​በቀጣይ  በጎንደር፣ በሐረር እና በድሬዳዋ ከተሞች የሚገነቡ ሆቴሎችን በማጠናቀቅ ለምረቃ እንደሚያበቃ ተጠቁሟል።  Source link
IMG_20260423_135546_721.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-24 02:18:37
የኢትዮጵያ ታምርት የአሥር ኪሎሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን መስፈርት እንዲሰጠው በቀጣዩ ዓመት እንደሚጠይቁ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ገለጹ ይኼ የተገለጸው የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አካል የሆነው፣ የ2018 ዓ.ም ኤክስፖ የአሥር ኪሎሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድርን አስመልክቶ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በጋራ ዛሬ ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ ነው። መግለጫውን የሰጡት በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አካል የሆነው የ2018 ዓ.ም ኤክስፖ የአሥር ኪሎሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አስተባባሪ አቶ አብድልፈታ የሱፍ፣ ሚኒስቴሩ ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር ስምምነት በማድረግ፣ ከዘንድሮ ጀምሮ የአገር አቀፍ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድርን መስፈርት እንዲያሟላ መደረጉን ገልጸዋል። በዚህም በውድድሩ የሚገኘው ውጤት ከአገር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲኖረው እየተሰራ መሆኑንና በቀጣዩ ዓመት ደግሞ የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን የአሥር ኪሎሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድርን መስፍርት እንዲያሟላ እንደሚደረግ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተሳትፎና ውድድር ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ጊዜ አድነው በበኩላቸው፣ ውድድሩ በዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እውቅና እንዲያገኝ ለማድረግ የሚከብድ ነገር አለመኖሩን፣ መስፈርቱን ማሟላት ብቻ...
IMG_20260423_193918_024.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-23 19:39:55
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia ለሰባተኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ከ 50.5 ሚሊዮን በላይ መራጮች መመዝገባቸው ተገለጸ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ50, 514,155 መራጮች መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም  ምሽት አስታወቀ የሰባተኛው ጠቅላላ የመራጮች ምዝገባ ትናንት ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ተጠናቋል The post ለሰባተኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ከ 50.5 ሚሊዮን በላይ መራጮች መመዝገባቸው ተገለጸ first appear on ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia and is written by በጋዜጣው ሪፓርተር Source link
IMG_20260423_193918_024.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-23 19:38:52
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ሕግን ባልተከተለ መንገድ ሲሰሩ አግኝቻቸዋለሁ ያላቸውን 22 የምርጫ ጣቢያዎች መዝጋቱን አስታወቀ።  ምርጫ ቦርድ እስካሁን ሲያከናውን የቆየውንና ከየካቲት 28 ቀን እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ሲያካሂድ የቆየውንና ዛሬ ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓም የተጠናቀቀውን የመራጮች ምዝገባን በተመለከተና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።  መግለጫውን የሰጡት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በአፈፃፀም ችግር ምክንያት የተዘጉ የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን ገልፀዋል። እነዚህ ምርጫ ጣቢያዎች በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በሀረሪ፣ በሲዳማና በሶማሌ ክልል እንደሚገኙ ተናግረዋል። የተዘጉት የምርጫ ጣቢያዎች ቁጥር በኦሮሚያ 12፣ በሲዳማ 2፣ በሶማሌ 6፣ በአማራ 1እና በሀረሪ 1 በአጠቃላይ 22 የምርጫ ጣቢያዎች መሆናቸውን አስረድተዋል። የመራጮች ምዝገባ ሲጀመር ቦርዱ ገጥሞት ከነበረው የቁሳቁስ ማጓጓዝና ሌሎች ችግሮች ባለፈ “መመዝገብ ያለባቸውን መራጮች ያለመመዝገብና መመዝገብ የሌለባቸውን የመመዝገብ ሂደት ነበር። በዚህም ቦርዱ እርምጃ ወስዷል። መዘጋት ያለባቸውን የምርጫ ጣቢያዎችም እንዲዘጉ አድርጓል” ብለዋል።  ትናንት ሚያዚያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት በተጠናቀቀው የመራጮች ምዝገባ 50,514,155 መራጮች መመዝገባቸውንና ከነዚህ መካከል በዲጂታል መንገድ የተመዘገቡ 5,503,561 መሆናቸውን፣ 45,010,594 የሚሆኑት ደግሞ በማኑዋል መመዝገባቸውን...
Culture-2.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-23 06:31:46
በእውነቱ ኃይሉ (ዶ/ር) በእንግሊዚኛ ቋንቋ ያዘጋጁት ‹‹UBUNTU-RULE Of FIVE›› የተሰኘው መጽሐፍ በባለፈው ሳምንት መገባደጃ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ራስ መኮንን አዳራሽ ለምረቃ በቅቷል፡፡ የመጽሐፉ ደራሲ በእውነቱ ኃይሉ (ዶ/ር) ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ብዙኃኑ ዕውቀቱን አይኖረውም፡፡ የሚያውቀውና የሚኖረው ሕይወት የተለያየ ነው፡፡ በመሆኑም የምናውቃቸውን ነገሮች የዕለት ከዕለት የእንቅስቃሴያችን አካል በማድረግ በሕይወታችን ውስጥ እንድናሰርፃቸው በማሰብ መጽሐፉ ሊዘጋጅ ችሏል ብለዋል፡፡ መጽሐፉ በተመረቀበት ወቅት ኡቡንቱ ቃሉን ወደ አማርኛ ስናመጣው ‹ሰው ሰው የሚሆነው በሰዎች መካከል ነው፣ ሰው ሰው ሆኖ የሚቆመው በሰዎች ነው› የሚል ትርጓሜ ያለው ነው ያሉት ደራሲው፣ ቋንቋ፣ ባህል፣ ትምህርት ወዘተ የመሳሰሉትን የምናገኘው ከሰዎች ነው፡፡ በተጨማሪም ዛሬ አለን ብለን የምንኮራበትን ዕውቀትንም ቢሆን ያገኘነው ከጓደኛ፣ ከመምህራንና ከማኅበረሰቡ ጭምር ነው፡፡ በመሆኑም ኡቡንቱ ‹‹እኔ፣ ዛሬን እኔ ሆኜ የተገኘሁት በማኅበረሰቡ ዕሴት ነው›› የሚል መልዕክት ያለው ነው ሲሉ አስታውቀዋል፡፡ መስፍን አርዓያ (ፕሮፌሰር)፣ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ‹ብዙዎቻችን ሰው መከበር አለበት እንላለን› ነገር ግን ይህን በተግባር እንተረጉመውም፡፡ አሁን አሁን ሰው መከበሩ ቀርቶ፣ አንዱ ለአንዱ ያሐመኖር ምክንያት እየሆነ ይገኛል፡፡ ከመከባበር ይልቅ መተናነቅ መገለጫችን...
Afar.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-23 06:30:42
ቅርስ ባለሥልጣን በ329 ሚሊዮን ብር ወጪ በአፋር ክልል ሙዚየም ለመገንባት ወደ ሥራ መግባቱን አስታውቋል፡፡ በአፋር ክልል በተለይም የአዋሽ ተፋሰስ፣ እንደ ሉሲ (ድንቅነሽ)፣ አርዲና ሰላም ያሉ ቅሪተ አካላት የተገኙበት ሥፍራ፣ በዓለም የሳይንስ ሊቃውንት ዘንድ ‹‹የሰው ዘር መገኛ›› (Cradle of Mankind) የሚል ስም ቢሰጠውም፣ እነዚህን ዓለም አቀፋዊ ሀብቶች በዝርዝር የሚያሳይና ታሪካቸውን በአግባቡ የሚተርክ ዘመናዊ ሙዚየም በአካባቢው ሳይገነባ ቆይቷል፡፡ የሙዚየሙ መገንባት ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ተመራማሪዎች ትልቅ የምርምር ማዕከል ሆኖ እንደሚያገለግል፣ ተመራማሪዎች ቅሪተ-አካላቱ በተገኙበት አካባቢ ሆነው ጥናት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጠር፣ የኢትዮጵያ ወጣት ተመራማሪዎች ከዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ጋር በቀጥታ እንዲገናኙና ልምድ እንዲቀስሙ መንገድ እንደሚከፍትም ባለሥልጣኑ አስታውቋል፡፡ ሙዚየሙ ለአፋር ማኅበረሰብ ከሕንፃ በላይ ትርጉም እንደሚሰጠው፣ ተገንብቶ ሲጠናቀቅም በክልሉ ያለውን የቱሪዝም ፍሰት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ጠቁሟል፡፡ ሙዚየሙ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ አፋርን የዓለም የሳይንስና የቱሪዝም ማዕከል በማድረግ፣ የሉሲን፣ የሰላምንና የአርዲን ዘላለማዊ ታሪክ ለትውልድ በሚያስተላልፍ መልኩ ጠብቆ ለማቆየት እንደሚያስችል ከባለሥልጣኑ ማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡ Source link
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-23 00:03:36
በመርሐፅድቅ መኮንን ዓባይነህ በፖለቲካው ዓለም ጥበብ የተመላበት ውሸት እንግዳና ያልተለመደ ነገር አይደለም፡፡ እንዲያውም አንዳንድ ወገኖች ይህንን ዓይነቱን የረቀቀ ውሸት ስሙን በማሳመር ዲፕሎማሲ ነው ሲሉ ሊያንቆለጳጵሱት ይቃጣቸዋል፡፡ እኔ እንኳ በዚህ የተጋነነ አቀራረብና የተዛባ ግንዛቤ መስማማት አብዝቶ ይቸግረኛል፡፡ ለማናቸውም በዚህ ረገድ ምድራችን ቁጥራቸው የበዛ ውሸታሞችን አስተናግዳለች፡፡ የአነስተኛና ጥቃቅን መንግሥታት ዋሾ መሪዎችን ለጊዜው እናቆያቸውና የታላቂቱ አገር የአሜሪካ አዛውንት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሳይቀሩ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በጥቁር ዓባይ ወንዝ ላይ የተገነባው ከአሜሪካ በተገኘ የፋይናንስ ድጋፍ ነው በማለት ዓይናቸውን በጨው አጥበው በአደባባይ ሲዋሹ ተመልክተናቸዋል፣ አድምጠናቸዋልም፡፡ ቀድሞ ነገር በውጊያ ላይ እንደነበሩ ሁሉ፣ ‹ጦር የተማዘዙትን ግብፅና ኢትዮጵያን አስታርቄ በመካከላቸው ሰላም አውርጃለሁ› ሲሉም በአራድኛው ልሳን አብዝተው ሲቀዱ ሰምተናቸዋል፡፡ ‹ቁቅም ከምንትስ ተቆጠረች› እንዲሉ አበው፣ በአንድ ጠባብ አካባቢ የሚስተዋል ችግር እንደ መሆኑ መጠን ያን ያህል ለንፅፅር ባይበቃም የዚህ አጭር ጦማር ባለቤት ለአሁኑ ማተኮር የፈለገው፣ ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጪ ግንባር (ትሕነግ) እያለ በሚጠራው ታጣቂ ኃይል ግብዝ መሪዎች ማለቂያ የሌለው ቅጥፈት ላይ ነው፡፡ ‹ዶሮ ብታልም ጥሬዋን ነው›...
taxi-1.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-23 00:02:28
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia እያጣጣምን! ዛሬ ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ከፊሉ በተንቧቸንበት ጎዳና ላይ ሲሮጥ፣ ከፊሉ ጉልበት ሳይከዳው ኑሮ ከብልኃቱ አልገናኝ ብሎት በጉብዝናው ወራት እያዘገመ ይጓዛል። ሩቅ ማሰብ፣ ነገን ማብሰልሰል፣ የዛሬን ሰላምና እርጋታ ያውካል። መንገድ ነውና ሰው መሆን በዘመናት ሒደት ሊፈታ ያልቻለ ታላቅ ሚስጥር ነውና ሕፃን አዋቂው ‹የዛሬ መንገዴ የት ያደርሰኝ ይሆን?› ብሎ ሲርበተበት ገጹ ላይ ይነበባል። በመኖር ብዙ ያስተዋሉ፣ ያሳለፉ፣ ክፉና ደግ ዕይታቸውን የለጠጠው አዛውንቶችና ጎልማሶች ጭንቀትና ሐሳብ የሚያጠወልጋቸውን ወጣቶች እያዩ ትናንትናቸው ውስጥ የቀሩ ሀቆችን በመገረም እያሰሉ ወዲያ ወዲህ ይላሉ። ያለፉበትን ጎዳና ሌላ ትውልድ፣ ሌላ አዲስ ፍጥረት በገዛ ራሱ ተሞክሮ እየዳሰሰ ሲያጣጥመው ሲያዩ፣ የሕይወት እንቆቅልሽ በዕድሜ ብዛት ጭምር የማይፈታ መሆኑን የሚገነዘቡ ይመስላሉ። መጪ ሂያጁን፣ መተላለፊያ ሰርጡን ሳይቀር ላጠና የሚመዘው ዕውቀት አያጣም። ከሚስተዋለው ትዕይንት በስተጀርባ የሚዘውረን ኃይል ሊሰጠን ያልሳሳው ነገር ቢኖር፣ በትዝብት የሚሰባሰብ የመረጃ ዕውቀት ሳይሆን አይቀርም። ጎዳናው በተመላላሹ የሐሳብ መጉላላት ተደበላልቋል። ይህ የሰው ልጅ መባዘን መስከኛው መቼ ይሆን? መልሱ የማይገደውን...
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-22 17:47:05
በኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪ ውስጥ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ 19ኙ የኢንሹራንስ ኩባንያዎች፣ በ2018 የሒሳብ ዓመት በዘጠኝ ወራት የዓረቦን ገቢያቸውን ከ42 ቢሊዮን ብር በላይ ማድረስ መቻላቸው ታወቀ። የዓረቦን ገቢያቸው በሒሳብ ዓመቱ መጨረሻ ከ50 ቢሊዮን ብር በላይ ይሆናል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡ ኩባንያዎቹ በ2018 የሒሳብ ዓመት በዘጠኝ ወራት ያስመዘገቡት የዓረቦን መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ36 በመቶ ብልጫ እንዳለው ከየኩባንያዎቹ የተገኘ አኃዛዊ መረጃ ለመረዳት ተችሏል። የዓረቦን ገቢያቸው ዕድገት በቀሪዎቱ ሦስት ወራትም በዚሁ መልኩ ከቀጠለ በሒሳብ ዓመቱ መጨረሻ ላይ ኢንዱስትሪው ለመጀመሪያ ጊዜ ከ50 ቢሊዮን ብር የዓረቦን ገቢ የሚያስመዘግብበት ዕድል ሊፈጠር እንደሚችል ያነጋገርናቸው የኢንሹራንስ ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡  በዘንድሮው የሒሳብ ዓመት በዘጠኝ ወራት ውስጥ ኢንዱስትሪው በጥቅል ካስመዘገበው 42.2 ቢሊዮን ብር የዓረቦን ገቢ ውስጥ 38.99 ቢሊዮን ብር የሚሆነው ሕይወት ነክ ካልሆነው የኢንሹራንስ ዘርፍ የተገኘ ነው፡፡  ከሁለቱ ዘርፎች ሌላ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በመስኮት ደረጃ እየተሰጠ ያለው የታካፉል ኢንሹራንስ ዘርፍ በዘጠኝ ወራት የዓረቦን ገቢው የ67 በመቶ ዕድገት በማሳየት 482 ሚሊዮን ብር የዓረቦን ገቢ ማሰባሰብ ችሏል፡፡  በሦስቱም የኢንሹራንስ ዘርፎች ከፍተኛውን ዓረቦን ገቢ...
TPLF.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-22 10:27:46
በጊዜያዊ አስተዳደርም ሆነ በጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት መቀጠል አያስፈልግም የሚል ውሳኔ ላይ የደረሰው ሕወሓት፣ በመጨረሻ ከጦርነቱ በፊት በተደረገው ምርጫ ተመሥርቶ የነበረው መንግሥት በትግራይ እንዲመለስ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ምርጫው በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና የተነፈገውና ሕገወጥ የተባለ መሆኑ ይታወሳል፡፡ ምርጫው ለትግራይ ጦርነት መጀመር አንዱ መነሻ ምክንያት መሆኑም ይታወቃል፡፡ ፌዴራል መንግሥት ምርጫውን ‹‹የጨረባ ምርጫ›› ብሎ ቢያወግዘውም፣ ሕወሓት ግን ወደ 2.8 ሚሊዮን የትግራይ ሕዝብ ድምፁን የሰጠበት፣ በሰፊ ብልጫ ሕወሓት አሸንፎ ክልላዊ መንግሥት የመሠረተበትና የድርጅቱ መሪ ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የክልሉ ፕሬዚዳንት የሆኑበት ‹‹ሕጋዊ ምርጫ›› መሆኑን ሲሟገት ቆይቷል፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳዳር ፕሬዚዳንት ሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ ማክሰኞ ማምሻ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫየሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ውሳኔ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትን ያፈርሳል ብለዋል ጦርነቱን ባስቆመው የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት መሠረት ከጦርነቱ በፊት ተመሥርቶ የነበረው መንግሥት እንዲፈርስና ጊዜያዊ አስተዳደር በትግራይ ክልል እንዲመሠረት፣ የስምምነቱ ፈራሚዎች ሕወሓትና ፌዴራል መንግሥቱ መግባባት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ በክልሉ ለሁለት ዓመታት ከቆየው ከአቶ ጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደር መፍረስ ወዲህ የፕሪቶሪያ ስምምነት መፍረሱን የሚጠቁሙ መግለጫዎች ከሕወሓት አመራሮች...
Translate »