Etiópia

Social-6-1.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-10 20:29:11
በዓልን የተለየ ድባብ እንዲኖረው ከሚያደርጉ ነገሮች አንዱ የቅርጫ ሥነ ሥርዓት ነው፡፡ ቅርጫ ለኢትዮጵያውያን የበዓል ማድመቂያ ብቻ ሳይሆን፣ የአንድነት፣ የኅብረትና የመተሳሰብ መገለጫም ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ በማኅበረሰቡ ዘመናት በተሻገረና በቆየ ልማድ መሠረት ለዓውደ ዓመት በሬ ገዝቶ በጋራ መቀራመት (ቅርጫ) የተለመደ ነው፡፡ የቅርጫ ድባብም የተለየ ነው፡፡ ጎረቤታሞች፣ ጓደኛሞች፣ ዘመዳሞች የሚሰባሰቡበት፣ ጨዋታ የሚደምቅበት፣ ጥሬ ሥጋ በተለይ ጉበት የሚበላበትና አረቄ የሚጠጣበትም ነው፡፡  አሁን ደግሞ ሰዎች በጋራ ተሰባስበው ከሚወስኑት የቅርጫ የእርድ ሥነ ሥርዓት ጎን ለጎን የኦንላይን የቅርጫ አገልግሎት እየተለመደ መጥቷል፡፡ ተቋማትም ቅርጫ ፈላጊዎች ሥፍራው መሄድ ሳያስፈልጋቸው ከቤታቸው ሆነው አገልግሎቱን የሚያገኙበትን ሁኔታ እየፈጠሩ ይገኛሉ፡፡ ‹‹የቅርጫ ማኅበራዊና ባህላዊ እሴቱ እንዲጠበቅ የቅርጫ ሥጋን ለደንበኞች እያቀረብን እንገኛለን፤›› የሚለው የኦንላይን ቅርጫ ከሚያቀርቡ ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆነው አጋፔ ነው፡፡ የአጋፔ ኦንላይን ቅርጫ ማኅበር መሥራችና ሥራ አስፈጻሚ እንደነገሩን፣  የኢትዮጵያውያን የቅርጫ ባህል፣ ማኅበራዊ ግንኙነትን የሚያጠናክርና የበዓል ድባብን አይረሴ ከሚያደርጉ እሴቶች አንዱ ነው፡፡ አሁን ላይ በተለይ በከተሞች አካባቢ እየተፈጠረና እየተስተዋለ የሚገኘው አዲስ የአኗኗር ዘይቤ፣ ሰዎች ከሚመስሏቸው ሰዎች ጋር ተሰባስበው ቅርጫ ማድረግ እንዳይችሉ አድርጓቸዋል፡፡ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች...
Ahmedin.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-10 20:27:33
ዘመናዊ የከተማ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችን በማስተዋወቅ የሚታወቀው አክሎክ ሞተርስ የተመሰረተው ከ20 ዓመት በፊት ነው፡፡ በአዲስ አበባ ‹‹አቫንዛ›› ታክሲዎችን ሥራ በማስጀመርና፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ የውሊንግ ተሽከርካሪዎችን አገር ውስጥ በመገጣጠም በቱሪስት ትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ተሠማርተው ለሚገኙ ግለሰቦችና ማኅበራት በማቅረብ ዘርፉ የተሻለ እንቅስቃሴ እንዲኖረው በማድረግ በኩልም የድርሻውን አበርክቶ እየተወጣ ይገኛል፡፡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን እየገጣጠሙ ስላሉበት ሁኔታ፣ የመለዋወጫ ዕቃዎችን ስለሚያመርቱበት ሒደትና በዘርፉ ላይ ስለሚያጋጥሙ ችግሮች የአክሎክ ሞተርስ መሥራችና ሥራ አስፈጻሚ እንዲሁም የኢትዮጵያ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪዎች ማኅበር ፕሬዚዳንት የሆኑትን አቶ አህመዲን መሐመድን የማነ ብርሃኑ አነጋግሯቸዋል፡፡ ሪፖርተር፡- አክሎክ ሞተርስ እንዴት ሊመሠረት ቻለ? አቶ አህመዲን፡- የተወለድኩት ትግራይ ክልል ውቅሮ ከተማ ነው፡፡ በወቅቱ አባቴ በአካባቢው የታወቀ ነጋዴ ነበር፡፡ ወፍጮ ቤቶችን በመትከልና በሌሎችም ንግዶች  የተሠማራ ነው፡፡ በጊዜው የነበረው የወፍጮ ቤቱ ሞተር በነዳጅ የሚሠራ በመሆኑ፣ ነዳጅ ሲጠፋና ሞተሩ ሲበላሽ ከከተማ ራቅ ካለ አካባቢ እህል ለማስፈጨት የሚመጡ ተገልጋዮች አንድና ሁለት ቀናት የሚጉላለጉበት አጋጣሚ ነበር፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ እኔ እጨነቃለሁ፡፡ በመሆኑም ሞተሩ ቶሎ እንዳይበላሽ የቅዳሜና እሑድ ቀናትን ሞተሩን ሰርቪስ የማድረግ ሥራ እሠራ...
ART.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-10 12:31:50
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia አዲሱ መጽሐፍ  ‹‹አካልን በብቃት›› በኢንስትራክተር ዳዊት መኰንን የተዘጋጀው  ‹‹አካልን በብቃት›› መጽሐፍ  መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ተመርቆ ለንባብ በቅቷል። ‹‹የስፖርት ማሽን አጠቃቀም›› እና ‹‹ስፖርት ያለመሣሪያ›› የተሰኙ ማንዋሎችን በማዘጋጀት ለተጠቃሚዎች ሲያሠራጭ እንደነበር  የገለጸው ኢንስትራክተር ዳዊት፣ አካልን በብቃት የተሰኘው መጽሐፍ  በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች መሄድ ለማይችሉ የኅብረተሰብ ክፍሎች ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አመልክቷል። መጽሐፉ ማንኛውም ሰው ባለበትና በተመቸው ቦታ ሆኖ ራሱን ብቁ እንዲያደርግ የሚያስችል ሳይንሳዊ  አሠራሮችን  አካትቷል። የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ከሥነ ምግብ መመሪያዎች ጋር አቀናጅቶ  የያዘም  ነው፡፡ The post አዲሱ መጽሐፍ  ‹‹አካልን በብቃት›› first appear on ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia and is written by በጋዜጣው ሪፓርተር Source link
ART-1.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-10 12:30:02
ሙዚቃን፣ ፋሽንን፣ ፊልምና ዲጂታል ጥበባትን ያካተተው የክራፍት አዲስ  ፓን አፍሪካ ፌስቲቫል ከሚያዝያ 22 እስከ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይካሄዳል። 20ኛ ዓመቱ ላይ የደረሰው ዘለማን  ኮሙኒኬሽን  ከአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽንና ፍሎውለስ ኢቨንትስ  ጋር በመተባበር በሚያከናወነው መድረክ፥ የዘርፉ ባለሙያዎችንና ተሳታፊዎችን በአንድ ላይ ያገናኛል ተብሎ ይጠበቃል። በተቋሙ ድረ ገጽ እንደተጠቆመው፣ ከመድረኩ  ትኩረቶች መካከልየፈጠራ ባለሙያዎች ሥራዎቻቸውን በቀጥታ ለገዢዎችና ለባለሀብቶች የሚያቀርቡበት የንግድ መድረክ መዘጋጀቱ አንዱ ሲሆን፣  ዲጂታል ጥበብና የፈጠራ ቴክኖሎጂዎች በኢኮኖሚው ላይ ያላቸውን ሚና የሚዳስሱ የባለሙያዎች ውይይትና ማስተር ክላሶች መኖራቸው ተጠቃሽ ነው። በዘርፉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱና አዳዲስ ፈጠራዎችን ላቀረቡ ባለሙያዎችም ልዩ ዕውቅናና የልህቀት ሽልማት ይሰጣል ተብሏል። የኢትዮ ጃዝ ፈጣሪው ሙላቱ አስታጥቄ ከለንደን ከሚመጣው ‘ስቴፕስ አሄድ’ (Steps Ahead) ባንድ ጋር በመሆን የሚያቀርበው ልዩ “የውርስ ኮንሰርት” (ሌጋሲ ኮንሰርት)  የፌስቲቫሉ አንዱ ክፍል ነው። የፊልም (ስማርትፊልም)፣ የቪዲዮ ጌም ውድድሮችና የዲጂታል ፍሪላንስ መድረኮች ላይ ወጣቶችና ሴቶች በስፋት እንዲሳተፉ ዕድል ይፈጥራል። ‹‹የሥነ ፈጠራ ጥበባት ለለውጥ›› በሚል መሪ ቃል  የሚካሄደውንፌስቲቫል አስመልክቶ መጋቢት 29 ቀን በተሰጠ መግለጫ፣  ዓላማው የአፍሪካን...
Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-09 20:16:16
በቶማስ በቀለ መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም. በሪፖርተር ያወጣሁት መጣጥፍ በአፄ ኃይለ ሥላሴ የመጨረሻው አሥር የሥልጣን ዓመታት ውስጥ ይሠሩ ስለነበሩት የግል እርሻ ሜካናይዜሽን ታሪክ እንደነበረ ይታወሳል። ታሪኩ በዋነኛነት የሚያጠነጥነው እነ አቶ (ኢንጂነር) ኃይሉ ሰብስቤ ስለመሠረቱት በመካከለኛው አዋሽ ይንቀሳቀስ ስለነበረው ሱብለሌ ስለሚባለው የግል እርሻ ሜካናይዜሽን ድርጅት ነበር። አንባቢያን ባቀረብኩት የድርጅቱና ከድርጅቱ ታሪክ በተጨማሪ አንዳንድ ተዛማጅና ስሜት ኮርኳሪ ታሪኮች የተወሰነ ግንዛቤ እንዳገኙ ተስፋ አደርጋለሁ። ዛሬ ደግሞ ከእርሻው ወጣ ብዬ በብረታ ብረት ኢንዱስትሪ ውስጥ ቀደምት ታሪክ ካላቸው ድርጅቶች መሀል የአንዱን ታሪክ ከዚህ በታች ላውጋችሁ። ዘለቀ በላይነህ ብረታ ብረት ሥራ ድርጅት በአንድ አጋጣሚ ባለቤቴ ከጓደኛዋ የተዋሰችውን መጽሐፍ ካነበበች በኋላ ‹‹ይህን መጽሐፍ አንብበው፣ በጣም ጥሩ መጽሐፍ ነው›› አለችኝ። እኔም አነበብኩት። የመጽሐፉ ርዕስ ‹‹ያልባከነ ዕድሜ›› የሚል ነው። የተጻፈው ወ/ሮ አመለወርቅ አበበ በሚባሉ ግለሰብ ነው። በነገራችን ላይ ወ/ሮ አመለወርቅ አበበ የቪኦኤ የአማርኛ ሬዲዮ ጣቢያ ተወዳጅ ጋዜጠኛ የነበረው የአቶ አዲሱ አበበ ታላቅ እህት ናቸው (ጋዜጠኛ አዲሱ አበበን ማንሳቴ ካልቀረ በ1970ዎቹ መጨረሻ ዓመታትና 1980ዎቹ ውስጥ ከጋዜጠኛ ሚሚ ስብሀቱ ጋር...
taxi-1024x504.png
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-09 20:15:11
በበዓል ዋዜማ ከጀሞ ወደ ፒያሳ ጉዞ ሊጀመር ነው። ‹‹እዚህ ጋ ጠጋ… ጠጋ… እህት እባክዎ ተጠጊላቸው…›› ተለምዷዊ የወያላ ቀጭን ትዕዛዝ ናት። ዛሬ ግን መብት አስከባሪ ገጥሞታል። ‹‹አልጠጋም፣ ለምንድነው የምጠጋው? በአንድ ወር ውስጥ ሁለቴ የነዳጅ ጭማሪ ተደርጎ  የተጋነነ ታሪፍ የከፈልኩህ እኮ ለአንድ መቀመጫዬ ብቻ ነው…›› ተጠጊ የተባለችው ወይዘሮ ብልጭ ብሎባታል። ‹‹ምናለበት ያለውን ችግር ተረድተን ወያላና መንግሥትን ከማማት እርስ በርስ ብንተባበር? የእኛ ነገር ተቀምጦ ሰማይ ቀዶ መስፋት ብቻ…›› ወያላው አጋዥ ለማግኘት አሳባሪ መንገዶችን በሙሉ በመጠቀም ላይ ነው። ‹‹እዚያ ያስለመዱህ ይጠጋጉልህ፣ ጊዜው የመጠጋጋት ነው ብለህ ከሆነ አላምንበትም…›› ወይዘሮዋ እንደ እንዝርት ሾራለች። ሹረቷን በመከፋት እያየ፣ ‹‹ምናለበት ብትጠጋና ብንቀሳቀስ? የእኛ ነገር እኮ ይገርማል…›› ይላል መሀል መቀመጫ የተቀመጠው ወጣት። ከኋላ ሦስተኛው ረድፍ ላይ ደግሞ፣ ‹‹ልክ ነሽ እንዳትሰሚው…›› እያለ አንድ ጎልማሳ ያጉተመትማል። ሁሉም ለራሱ ልክ ነው ያለውን አስተያየት እየሰጠ ጉዞ ሊጀመር ነው፡፡ ልዩነት ለዘለዓለም ይኑር! ጎልማሳው አጠገብ ከአዲስ ስልኳ ጋር በፍቅር የወደቀች የምትመስል የጠይም ቆንጆ ተቀምጣለች፡፡ መጨረሻ ወንበር አንድ አዛውንት፣ አንድ ጎልማሳና ዕድሜያቸው በሃያዎቹ አጋማሽ የሚገመቱ ወጣቶች ጎን...
bUSINESS-2.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-09 06:11:01
በዓለም አቀፍ ደረጃ የተፈጠረው የነዳጅ እጥረትና የዋጋ ጭማሪ በሁሉም የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ እያሳረፈ ያለው ተፅዕኖ በግልጽ እየታየ ቢሆንም፣ የግንባታ (የኮንስትራክሽን) ዘርፉ ላይ የበለጠ ተግዳሮት እንደሚፈጥር ተሠግቷል፡፡ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከፍተኛ የሚባለውን የሰው ኃይል በመያዝ የሚጠቀሰው የኮንስትራክሽን ኢንዱትሪ ከነዳጅ እጥረትና ዋጋ ንረት ጋር ተያይዞ የገጠመው ፈተና ከዘርፉ አልፎ አጠቃላይ የአገሪቱን ኢኮኖሚ ሊጎዳ እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች ሥጋታቸውን ይገልጻሉ፡፡ ከግንባታ ፕሮጀክቶች ጠቅላላ ወጪ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘው የነዳጅ ወጪ መሆኑን የሚገልጹት ያነጋገርናቸው የዘርፉ ባለሙያዎች፣ በአሁኑ ወቅት በመካከለኛው ምሥራቅ ከተቀሰቀሰው ጦርነት ጋር ተያይዞ ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጠረው የነዳጅ እጥረትና የዋጋ ጭማሪ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ የግንባታ ሥራዎቻቸውን እስከማቆም የሚደርስ ዕርምጃ ሊያስወስዳቸው እንደሚችል አመልክተዋል፡፡ የኢትዮጵያ የሥራ ተቋራጮች ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት ግርማ ኃብተ ማሪያም (ዶ/ር) ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የመካከለኛው ምሥራቅ ቀውስ በነዳጅ ምርት አቅርቦት ላይ የፈጠረው ተግዳሮት በኢትዮጵያ ላይ ብቻ የመጣ ባይሆንም የጉዳቱ መጠን ግን እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች ላይ ከፍተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ተዋናዮች ለግንባታ ሥራዎቻቸው ወሳኝ የሆነውን የነዳጅ አቅርቦት በበቂ ሁኔታ ማግኘት ካልቻሉ የጀመሯቸውን የግንባታ...
photo_2026-04-08_15-07-07.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-09 06:09:57
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አስጠነቀቀ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኅብረተሰቡ የትንሳዔ በዓል ምክንያት በማድረግ በብዛት ለገበያ የሚቀርቡ ምግቦች ላይ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳሰበ፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በመደበኛና በዘመቻ በተደረገ ክትትል በምግብና ጤና ነክ ዘርፍ በ21,361 ተቋማት፣ በ4,105 ጤና ነክ ተቋማት እንዲሁም በ1,293 የመድኃኒት ችርቻሮ ድርጅቶች ላይ ፍተሻ ማድረጉን የባለስልጣኑ ቁጥጥር ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ እንጋ እርቀታ ተናግረዋል። ከስታንዳርድ በታች ሆነው በተገኙ 1,230 የምግብ ተቋማት ፣ 187 የጤና ተቋማትና 68 የመድኃኒት ተቋማት እንዲሁም አራት የጤና ባለሙያዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን አስታውቀዋል። በተጨማሪም በ25,485 ተቋማት ላይ የትንባሆ ቁጥጥር በማድረግና በ1,366 የመንግሥትና የግል ጤና ተቋማት ላይ ክትትል በማድረግ፣ በአጠቃላይ ከ123 ሚሊዮን ብር በላይ (78.3 ሚሊዮን ብር የምግብ፣ 39.6 ሚሊዮን ብር የመድኃኒትና 5.9 ሚሊዮን ብር የትንባሆ ውጤቶች ግምታዊ ዋጋ ያላቸውና ለጤና አደገኛ የሆኑ ምርቶችን ከገበያ እንዲወገዱ መደረጉን አቶ አቶ እንጋ ተናግረዋል። ከትንሳኤ በዓል ጋር ተያይዞ ኅብረተሰቡ በበዓላት ወቅት በብዛት የሚሸምታቸውን እንደ ዘይት፣ ቅቤ፣...
Politics-2.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-08 07:00:43
ማክሰኞ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ረፋድ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በይፋዊ ማኅበራዊ ትስስር ገጾቹ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ከሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ ጋር ያደረጉትን ግንኙነት መግለጹ ይታወሳል፡፡ ጊዜያዊ አስተዳደሩን ከተረከቡ አንድ ዓመት የሞላቸው ሌተና ጄኔራል ታደሰ በኃላፊነት የመቆያ ጊዜ ገደባቸው ዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚጠናቀቅ በመሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ የትግራይ ክልልን አስመልክቶ የሚነሱ ፖለቲካዊ ጥያቄዎች በርክተው ከመሰማታቸው አኳያ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የሚያደርጉት ግንኙነት በእጅጉ ተጠባቂ ሆኖ ነበር የሰነበተው፡፡ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ዕጣ ፈንታ በሚመለከት ምን ዓይነት ውሳኔ እንደሚተላለፍ፣ የትግራይ በጀት መለቀቅ ጉዳይን አስመልክቶ፣ የነዳጅ አቅርቦትን፣ የተፈናቃዮችን መመለስ፣ የወሰን ጉዳይ መፈታትን፣ እንዲሁም የምርጫና አገራዊ ምክክር ጉዳዮችን በሚመለከቱ አጀንዳዎች ላይ ምን ዓይነት ውሳኔ ይተላለፋል የሚለው ምላሽ ከዚህ ግንኙነት ሲጠበቅም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መግለጫ ከጥቂት ፎቶግራፎችና ከአጭር ድምፅ አልባ ቪዲዮ ጋር አጅቦ፣ ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዓመታዊ የአፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦላቸው...
photo_2025-05-10_16-36-51.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-08 06:59:26
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia [ክቡር ሚኒስትሩ በቅርቡ የማጭበርበር ተግባር ሲፈጽሙ ነበር ተብለው በቁጥጥር ሥር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን በተመለከተ ከአማካሪያቸው ጋር እየተጨዋወቱ ነው] ክቡር ሚኒስትር በእኛ በኩልም ትልቅ ችግር ያለ ይመስለኛል። በእኛ በኩል ማለት? በመንግሥት በኩል ማለቴ ነው። እንዴት… ምን ችግር አለ? ክቡር ሚኒስትር ፖሊስ በዚህ ጉዳይ ላይ ምርመራ አድርጎ ያረጋገጠውን ስሰማ ማመን ነው ያቀተኝ። ምኑን ነው ማመን ያቃተህ? ድርጅቱ ከውጭ አገር ያስመጣቸው ናቸው ተብለው ሲተዋወቁ የነበሩ ተሽከርካሪዎች ጉዳይ። የገቡት ተሽከርካሪዎች ችግር ያለባቸው ናቸው? አይደሉም? እና ምኑ ነው ያስደነቀህ? ከውጭ የገቡ አይደሉም። ምን? ክቡር ሚኒስትር ከውጭ ያስገባቸው አይደሉም። እና ከየት የመጡ ናቸው? ከአገር ውስጥ በውሰት ሰብስቦ ነው። አይደረግም! እንደዚያ ነው የሆነው ክቡር ሚኒስትር። ሊሆን አይችልም! በእኛ በኩል ችግር አለ ያልኩት እኮ ለዚያ ነው። ምንድነው በእኛ በኩል ያለው ችግር? ክቡር ሚኒስትር ከውጭ የሚገቡ ተሽከርካሪዎችን የሚመዘግቡ ተቋማት አሉን አይደለም እንዴ? አዎ። እነዚህ ተቋሞቻችን በዚህ ድርጅት ስም ተሽከርካሪ ገብቶ ከሆነ ያውቃሉ፣ ይመዘግባሉ። አይደለም? ልክ ነው። ነገር ግን ይህን...
Translate »