Etiópia

Politics-77-2.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-05-20 15:58:35
የምሥራቅ አፍሪካ አገሮች ከመከፋፈል ይልቅ መተባበር እንዳለባቸው፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ አሳሰቡ፡፡ አቶ ጌታቸው ማሳሰቢያውን የሰጡት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ዘላቂ ሰላም፣ ፀጥታና ቀጣናዊ ውህደት ለማጠናከር ያለመ ከፍተኛ የፖለቲካ መሪዎች፣ የምሁራንና የዲፕሎማቶች የጋራ የምክክር መድረክ (Horn Inter-Elite Dialogue) በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅግጅጋ ሲካሄድ ነው፡፡ በመድረኩ መክፈቻ ላይ የተገኙት አቶ ጌታቸው ረዳ ባደረጉት ንግግር፣ ‹‹ዛሬ የተፈጥሮ ባህሪያትና ተለዋዋጭነት ለቁሳዊው ዓለማችን ምን ትርጉም እንዳለውና ስለምናከናውናቸው ነገሮች ባህሪ መናገር እፈልጋለሁ፤›› ብለዋል። አማካሪው አክለውም በዜጎች መካከል ሊኖር ስለሚገባው ትስስር ሲያስረዱ፣ ‹‹አብዛኞቻችን ከአንድ በላይ የሆኑ ማኅበረሰቦች፣ እርስ በርስ ለመደጋገፍ፣ አጋር ለመሆን፣ ተደጋጋፊ ለመሆንና መሪ ለመሆን ሌሎች ማኅበረሰቦች የሚኖሩበትን እንዲህ ዓይነቱን ዓለም ለመፍጠር የተስፋ ስሜት አለን ብዬ አስባለሁ፤›› ብለዋል።  አቶ ጌታቸው፣ መሪዎች ማኅበረሰቡን ወደ መከፋፈል በሚወስዱ አጀንዳዎች ላይ ከማተኮር ይልቅ፣ በትክክል ትርጉም ባላቸውና ቀጣናውን በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ሕዝቡ በመሪዎቻቸው ላይ ጫና ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። በመድረኩ ለውይይት የተመረጡት ጭብጦች በጣም ወቅታዊና ተገቢ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ጌታቸው፣ በቀጣይ ውይይቶችም ላይ፣ ‹‹አዳዲስ...
Politics-77-2.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-05-20 15:58:34
የምሥራቅ አፍሪካ አገሮች ከመከፋፈል ይልቅ መተባበር እንዳለባቸው፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ አሳሰቡ፡፡ አቶ ጌታቸው ማሳሰቢያውን የሰጡት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ዘላቂ ሰላም፣ ፀጥታና ቀጣናዊ ውህደት ለማጠናከር ያለመ ከፍተኛ የፖለቲካ መሪዎች፣ የምሁራንና የዲፕሎማቶች የጋራ የምክክር መድረክ (Horn Inter-Elite Dialogue) በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅግጅጋ ሲካሄድ ነው፡፡ በመድረኩ መክፈቻ ላይ የተገኙት አቶ ጌታቸው ረዳ ባደረጉት ንግግር፣ ‹‹ዛሬ የተፈጥሮ ባህሪያትና ተለዋዋጭነት ለቁሳዊው ዓለማችን ምን ትርጉም እንዳለውና ስለምናከናውናቸው ነገሮች ባህሪ መናገር እፈልጋለሁ፤›› ብለዋል። አማካሪው አክለውም በዜጎች መካከል ሊኖር ስለሚገባው ትስስር ሲያስረዱ፣ ‹‹አብዛኞቻችን ከአንድ በላይ የሆኑ ማኅበረሰቦች፣ እርስ በርስ ለመደጋገፍ፣ አጋር ለመሆን፣ ተደጋጋፊ ለመሆንና መሪ ለመሆን ሌሎች ማኅበረሰቦች የሚኖሩበትን እንዲህ ዓይነቱን ዓለም ለመፍጠር የተስፋ ስሜት አለን ብዬ አስባለሁ፤›› ብለዋል።  አቶ ጌታቸው፣ መሪዎች ማኅበረሰቡን ወደ መከፋፈል በሚወስዱ አጀንዳዎች ላይ ከማተኮር ይልቅ፣ በትክክል ትርጉም ባላቸውና ቀጣናውን በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ሕዝቡ በመሪዎቻቸው ላይ ጫና ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። በመድረኩ ለውይይት የተመረጡት ጭብጦች በጣም ወቅታዊና ተገቢ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ጌታቸው፣ በቀጣይ ውይይቶችም ላይ፣ ‹‹አዳዲስ...
Abiy.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-05-20 09:06:56
‹‹ዳታን እንደ ወርቅ፣ እንደ ሀብት ከሥር ከመሠረቱ ዓይተን፣ በዚያ ጉዳይ ገዶን መክረን፣ ዘክረን፣ አውቀን ለመምራት የምንገለገልበት ዋናው ምክንያት፣ ራዕያችን ጠንካራ አገረ መንግሥት መገንባት ነው፤›› ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ ጠንካራ አገረ መንግሥት ለመገንባት ከሚያስፈልጉ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል አንዱ ሉዓላዊነት መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ነገር ግን ሉዓላዊነት ሲባል የኢትዮጵያን ድንበር መከላከል ብቻ ሳይሆን የመረጃ፣ የምግብ፣ የፖሊሲና ሌሎች ዘርፎች ሉዓላዊነት ጭምር መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ጋር በመሆን፣ ‹‹የዳታ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት›› በሚል መሪ ሐሳብ ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም. የብሔራዊ ጉባዔና ኤግዚቢሽን የመክፈቻ መድረክ ላይ ነው፡፡ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ መረጃን ገዝቶና ተውሶ ማረጋገጥ እንደማይቻልና ለማንኛውም ፖሊሲ ዋነኛ ግብዓት የሆነውን መረጃን መግዛት ስለተቻለ ብቻ በመግዛት ወይም ስለተገኘ ብቻ በመዋስ ፖሊሲ ቢቀረፅ፣ ፖሊሲው በተሟላ መንገድ የአገሪቱን ፍላጎት ሊያሳካ የሚችል ነው ብሎ መውሰድ እንደሚያስቸግር ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም የራስን መረጃ ማከማቸትና መተንተን መቻል ለፖሊሲ ሉዓላዊነት እንደ ትልቅ ግብዓት ይወሰዳል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ያላትን አቅምና ሀብት በሚገባ ካላወቀን በበቂ ለመገበያየት፣ የውጭ...
Politics-66-1.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-05-20 09:05:43
‹‹ሪፖርቱ እውነት መሆኑን አምነውና ፈርመው ከተቀበሉት አካላት አንዱ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ነው››      የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛውን አገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ፣ የፀጥታ ሁኔታዎችን ለመከታተል የተሰማራው ቡድን፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ከ97 በመቶ በላይ ምርጫ ለማካሄድ አስቻይ ሁኔታ አለ ብሎ ያቀረበውን ሪፖርት፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ውድቅ እንዲያደርገው ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ ጥሪ አቀረበ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሪፖርተር በሰጠው ምላሽ፣ ምርጫ ለማድረግ አስቻይ ሁኔታ መኖር አለመኖሩን ለማጣራትና ለመከታተል ከተሰማራው ቡድን ጋር ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ አብሮ የነበረና በተገኘውም ውጤት ተስማምቶ የሪፖርቱ አካል መሆኑን አስረድቶ፣ ውድቅ ይደረግ የሚለውን ጥያቄ እንደማይቀበለው ተናግሯል፡፡ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ይህን ማሳሰቢያ የሰጠው ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ትላንት ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፡፡ የትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ጌትነት ወርቁ በሰጡት መግለጫ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕናና አካባቢው ባሉ ወረዳዎች በሲስተም ችግር ምክንያት ከ15 በላይ የትብብሩ ዕጩዎች ሳይመዘገቡ እንደቀሩ ገልጸዋል። የትብብሩ ዋና ጸሐፊ ምስጢረ ሥላሴ ታምራት በበኩላቸው፣ እናት ፓርቲ ትብብሩን ከመቀላቀሉ በፊት፣...
Politics-1-1.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-05-18 16:01:05
ከሰሞኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የፖለቲካ ጉዳዮች ምክትል ጸሐፊ ከሆኑት አሊሰን ሁከር ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ሴትየዋ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አራተኛዋ ቁልፍ ሥልጣን ያላቸው ሲሆኑ፣ የአገራቸውን የሁለትዮሽ ግንኑኘት የተመለከቱ ጉዳዮችን የሚመሩ እንዲሁም የአፍሪካ፣ የምሥራቅ እስያና የፓስፊክ ውቅያኖስ፣ የአውሮፓና ምሥራቅ አውሮፓ፣ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ እነሱ የቅርብ ምሥራቅ የሚሉት (የመካከለኛው ምሥራቅ)፣ ደቡብና ደቡብ ምሥራቅ እስያ፣ የምዕራባዊ ንፍቀ ክበብ ቀጣና ጉዳዮችን የሚመለከቱ ቢሮዎችን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ የሚከታተሉ ወሳኝ ሥልጣን ያላቸው ናቸው፡፡ ይህ አዲስ ስምምነትም ‹‹Bilateral Structured Dialogue Framework (BSD)›› የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፣ እንዲህ ያለው ስምምነት የሚፈረመው ደግሞ በመሠረታዊነት የሁለትዮሽ ግንኙነትን ቅርፅና መልክ ለማስያዝ ሲፈለግ እንደሆነ የተለያዩ የመረጃ ምንጮች አመልክተዋል፡፡ ይህ ስምምነት በዋናነት አራት መሠረታዊ አንጓዎችን ማጠንጠኛው ያደረገ እንደሆነም ታውቋል፡፡   የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ምክትልና የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ አሊሰን ሁከር ጋር የመጀመሪያው ኢትዮጵያ በሕዝብ ብዛት፣ በወታደራዊ፣ በጂኦግራፊም ሆነ በሌላ መመዘኛ በቀጣናው ጠንካራ ተፅዕኖ ያላት አገር (Ethiopia as an...
1-e1779115899728.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-05-18 15:59:38
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia የአፍሪካ ቀንድ ልሂቃን የውይይት መድረክ በሶማሌ ክልል ተጀመረ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ሠላምና ደህንነት ላይ የሚመክረው የአፍሪካ ቀንድ ልሂቃን የውይይት መድረክ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ዛሬ ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓም መካሄድ ጀመረ። መድረኩ በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ፣ በሴንተር ፎር ሪስፖንሲብል ኤንድ ፒስፉል ፖለቲክስ (CRPP) እና በሶማሌ ክልል መንግሥት በጋራ የተዘጋጀ ሲሆን ፣ የኢትዮጵያ ፣ የሶማሊያ ፣ የጅቡቲ እና የኬንያ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት እንዲሁም የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ዋና ጸሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) እና የቀጣናው ልሂቃን እየተሳተፉበት ይገኛሉ። ፎቶ በ፦ መስፍን ሰለሞን / ሪፖርተር “ለአፍሪካ ቀንድ ስትራቴጂካዊ ነፃነትና ዘላቂ ሰላም ክልላዊ ኤጀንሲን ማጠናከር” በሚል መሪ ቃል መካሄድ የጀመረው ይህ የውይይት መድረክ ፣ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ስትራቴጂካዊ ነፃነትን፣ ክልላዊ ውህደትንና ዘላቂ ሰላምን ለማራመድ ያለመ ነው። የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ፣ በአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ሰላምን ማረጋገጥ የሚቻለው በፍላጎት ሳይሆን ተቋማዊ አሠራርን በመትከል፣...
Dialoug.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-05-18 09:15:34
የአጀንዳ ማርቀቅ ሥራው በረቂቅ ደረጃ መጠናቀቁ ተገልጿል የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን በቀጣይ በጀት ዓመት ለሚያከናውናቸው ሥራዎች 2.6 ቢሊዮን ብር በጀት እንደሚያስፈልገው ለፓርላማ አስታወቀ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የ2019 በጀት ዓመት የበጀት ፍላጎት ገምግሟል፡፡ በግምገማው ወቅት የበጀት ጥያቄውን ለቋሚ ኮሚቴው ያቀረበው የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ በቀጣይ በጀት ዓመት ለሚያከናውናቸው ቀሪ ሥራዎች 2.6 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው መግለጹን የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ አቶ ጥበቡ ታደሰ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽኑ በዋናነት የቀረው ሥራ የምክክር ጉባዔውን ማካሄድ መሆኑንና በጉባዔው ላይም 4,000 የሚጠጉ ተወካዮች እንደሚሳተፉ የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ ለተሳታፊዎች የሚያስፈልገው ወጪ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ተወካዮቹ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተመካክረው መግባባት ላይ ለመድረስ የሚወስድባቸው ጊዜ እንደሚኖር፣ የበጀት ጥያቄው የቀረበውም በአዲስ አበባ ለሚኖራቸው ቆይታ ለሚያስፈልጋቸው የማረፊያ፣ የምግብ፣ የጤና አገልግሎት፣ የአዳራሽ ኪራይ፣ ከየአካባቢያቸው የሚመጡበት ትራንስፖርትና በአዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታ ደግሞ ከመሰብሰቢያ ቦታቸው ወደ ማረፊያቸው ለሚያደርስ የትራንስፖርት አገልግሎት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የበጀት ፍላጎቱን የገመገመው የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ኮሚሽኑ ያቀረበው...
Social-2-1.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-05-18 09:14:27
የሕፃናት አስተዳደግ ልማድና ባህል በርካታ አዎንታዊና አብሮነትን የሚያጎለብቱ ገጽታዎች ቢኖሩትም፣ በውስጡ የያዛቸውና ዛሬም ድረስ በልጆች ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ አሉታዊ ጥላ የሚያጠሉ ልማዳዊ አሠራሮች አልጠፉም። በበርካታ አካባቢዎች ሕፃናት ‹‹ሥርዓት እንዲይዙ›› በሚል በወላጆቻቸውና በአሳዳጊዎቻቸው በኃይል ይገረፋሉ፣ ይቆነጠጣሉ። ሕፃናት ለከፋ የጉልበት ብዝበዛ ይጋለጣሉ፡፡ ከዚህም ባሻገር በርካታ ሕፃናት ትምህርት ቤት ገብተው በሚማሩበትና አዕምሯቸው አዳዲስ ነገሮችን በሚቀበልበት ወሳኝ ዕድሜ ላይ ሆነው፣ ማወቅ የሚገባቸውን መሠረታዊ ዕውቀትና ክህሎት ሳያውቁና ሳይጨብጡ የሚቀሩበት አጋጣሚ ሰፊ ነው።  አሳሳቢ እየሆነ የመጣው ጉዳይ ደግሞ ወደ ትምህርት ቤት ሄደው በከፍተኛ የረሃብና የሥርዓተ ምግብ እጥረት ምክንያት ትምህርታቸውን በአግባቡ መከታተል የማይችሉ ሕፃናት ቁጥር ቀላል አለመሆኑ ነው። መንግሥት እነዚህንና መሰል ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት በሚል ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ በአገር አቀፍ ደረጃ የተማሪዎች የምገባ ሥርዓት በማቋቋም በተመረጡ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተግባራዊ ሲያደርግ ቆይቷል። እስካሁንም  ከ35 ሺህ በላይ በሚሆኑ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የምገባ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል። ‹‹የቀዳማይ ልጅነት ክብካቤና ትግበራ›› በሚል  ትምህርት ሚኒስቴር፣ የጤና ሚኒስቴር እንዲሁም የሴቶች፣ ሕፃናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋራ በመቀናጀት‹‹የኢትዮጵያ የቀዳማይ ልጅነት...
Election-2.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-05-18 02:33:36
በኢትዮጵያ ለረዥም ዓመታት ያህል ሳይካሄድ የቆየው የአካባቢ ምርጫ፣ ለመልካም አስተዳደር ምንጭ በመሆኑ በጠንካራ ሕጋዊ መሠረት ወቅቱን ጠብቆ ሊካሄድ እንደሚገባው ተገለጸ፡፡ ለመጨረሻ ጊዜ በ2005 ዓ.ም. የተካሄደውን የአካባቢ ምርጫ ቀጠሮ እየተያዘለት ለ13 ዓመታት ሳይካሄድ ቆይቷል፡፡ መልካም አስተዳደር ለአፍሪካ የተሰኘው የአፍሪካ ቀንድ ቅርንጫፍና በአዲስ አበባ የሚገኘው መሥሪያ ቤት ከ7ኛው አገራዊ ምርጫ ጋር የተገናኘውን ሦስተኛ ዙር  መድረኩን አካባቢ ምርጫን የተመለከተ ውይይት አካሂዷል፡፡ ‹‹የአካባቢ አስተዳደሮችን ማጠናከር ለመልካም አስተዳደር ያለው ሚና›› በሚል የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች፣ ምሁራንና ሌሎች ተሳታፊዎች በተገኙበት የፓናል ውይት የተካሄደው ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ነው፡፡ በመድረኩ የአካባቢ አስተዳደሮች አስፈላጊነት ለመልካም አስተዳደር ያላቸው ጠቀሜታና ወቅታዊ ሁኔታ በኢትዮጵያ በሚል የመነሻ ጽሑፍ ያቀረቡት፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፌዴራልና አስተዳደር ጥናት ማዕከል መምህሩ ዘመላክ አይተነው (ዶ/ር) ናቸው፡፡ ተመራማሪው በጽሑፋቸው የአካባቢ መንግሥታት ብዙ ትኩረት የማይሰጣቸው ነገር ግን ለመንግሥት አገልግሎት ፍትሐዊነት መሠረት ያላቸው መዋቅሮቸር  ናቸው ብለዋል፡፡ የማዕከላዊ መንግሥት በወደቀና በተተራመሰ ጊዜ የአካባቢ መንግሥታት ጠንክረውና ራሳቸውን ችለው የሚቆሙ ናቸው የሚሉት ተመራማሪው፣ ለዚህም ሶማሊያ ትልቅ ምሳሌ እንደሆነች ያብራራሉ፡፡ በኢትዮጵያ...
Melatewerk.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-05-18 02:32:33
ተጨማሪ 9.7 ቢሊዮን ጠይቋል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለምርጫ ሥራው ከለጋሽ አካላት ይገኛል በሚል በዕቅድ ይዞት የነበረው ገንዘብ ባለመገኘቱ፣ አብዛኛው ወጪ በመንግሥት መሸፈኑን አስታወቀ፡፡ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ ለ2018 ዓ.ም. ምርጫ በጀት ያስፈልጋል ተብሎ ተጠይቆ የነበረው 15 ቢሊዮን ብር ቢሆንም፣ ከአጋር ድርጅቶች ይገኛል በሚል ወደ 10.8 ቢሊዮን ብር ዝቅ ያለ በጀት አንደተደለደለለት ገልጸዋል፡፡ በዚህም የበጀት ውስንነት ምክንያት ከዚህ ቀደም ከተመደበለት በተጨማሪ ለቀሪ ሥራዎቹ 9.7 ቢሊዮን ብር አዲስ በጀት በመጠየቅ፣ አጠቃላይ የቦርዱን የምርጫ ወጪ  ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ አሳልፎታል፡፡ ሰብሳቢዋ ይህን የተናገሩት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቦርዱን የፋይናንስ አጠቃቀምና የመጪውን በጀት ዓመት ዕቅድ በተመለከተ ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ በመግለጫቸው ለምርጫው የአጋር ድርጅቶች ድጋፍ እ.ኤ.አ. ከ2022 እና እ.ኤ.አ. 2023 ከነበረው ያነሰ የነበረ በመሆኑ፣ ያንን በመረዳት ለተያዘው ምርጫ ወደ 15 ቢሊዮን ብር ለማሳደግ ታስቦ የነበረ ቢሆንም፣ ድጋፍ ሊመጣ ይችላል በሚል በጀቱ ዝቅ ብሎ መበጀቱን ተናግረዋል፡፡ ‹‹በዚህ ጊዜ ያለው የአጋር ድርጅቶች ድጋፍ በጣም ዝቅተኛ...
Translate »