Etiópia

Social-00.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-08-10 10:35:04
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ታሪክ ረዥምና የጎላ ቢሆንም፣ በየጊዜው ከሚቀያየረው ዓለም አቀፋዊ የጂኦ ፖለቲካ ሁኔታ ጋር ተፎካካሪ ሆኖ ለመቀጠልና የአገርን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር የወጣቶች ሚና አስፈላጊ እንደሆነ ይነገራል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ኅብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሲኤ) እና የበርካታ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መቀመጫ እንደመሆኗ በዲፕሎማሲው መስክ የተካኑና የነቁ ወጣቶች ያስፈልጓታል። ይህንን ዕውን ለማድረግ በሚል የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት በቅርቡ የወጣቶችን ዕውቀትና ክህሎት ለማሳደግ ያለመ የክረምት ሥልጠና ፕሮግራም ቀርፆ እየተገበረ ይገኛል። በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የባለድርሻ አካላት ሥልጠና ዳይሬክተር ጄኔራል የሆኑት አቶ መላኩ ሙሉዓለም ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ኢንስቲትዩቱ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲስ ለሚቀላቀሉ፣ በሥራ ላይ ላሉና ወደ ውጭ አገር ለሚመደቡ ዲፕሎማቶች ሥልጠና ከመስጠት ባለፈ ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ያከናውናል።  የአገር ውስጥ ባለድርሻ አካላት የሚባሉት ወጣቶች፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትና የሌሎች ሚኒስቴሮች ሠራተኞች ሲሆኑ፣ ለእነዚህ አካላት በተለይ ከፕሮቶኮል ጋር የተያያዙ ሥልጠናዎች ይሰጣሉ። የውጭ አገር ባለድርሻ አካላትን በተመለከተ ደግሞ የጎረቤት አገሮች ዲፕሎማቶችን ያቀፈ መሆኑን የተናገሩት አቶ መላኩ፣ በቅርቡ የደቡብ ሱዳን ዲፕሎማቶችን አምጥቶ ማሠልጠኑን...
Social-44.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-08-10 10:34:02
 በከሰል ምርትና ዝውውር ላይ ቁጥጥር እንደሚደረግም ተገልጿል በአዲስ አበባ ከተማ የድምፅ ብክለት በሚያደርሱ ተቋማት ላይ ይጣል የነበረው ቅጣት ከፍ ብሎ መመርያው ማሻሻያ ሊደረግበት መሆኑን፣ የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና አማካሪና የአካባቢ ብክለትና አየር ንብረት ለውጥ ዘርፍ ተወካይ አስተባባሪ አቶ አዱኛ ወንድሙ፣ ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶ ክትትልና ቁጥጥር ከሚያደርግባቸው የአካባቢ ብክለት መንስዔ ዓይነቶች መካከል አንዱ የድምፅ ብክለት ነው ብለዋል፡፡ ይህ የብክለት ዓይነት የሚያስከትለው ቅጣት አነስተኛ መሆን ችግሩ እንዲባባስ ማድረጉን ተናግረዋል። ተቋሙ የብክለት ቁጥጥር አዋጅን መሠረት በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደረጃ የሚተገበር መመርያ ማዘጋጀቱን ለሪፖርተር ገልጸዋል። መመርያው የችግሩን አሳሳቢነት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የድምፅ ብክለት በሚያደርሱ ተቋማት ላይ ከዚህ በፊት ይጣል በነበረው አስተዳደራዊ ቅጣት ማሻሻያ የተደረገበት መሆኑን፣ አቶ አዱኛ ጨምረው ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት ከድምፅ ብክለት ጋር ተያይዞ የሚጣለው ቅጣት አነስተኛ መሆኑንና ትንሹ ቅጣት አምስት ሺሕ ብር ሲሆን፣ ትልቁ ደግሞ 25,000 ብር እንደሆነ ተናግረዋል። ይህንን የቅጣት እርከን የሚያሻሽልና የብክለት ቁጥጥር አዋጅን መሠረት ያደረገ መመርያ...
ELPA-00.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-08-10 02:23:39
6 ቢሊዮን ብር ወጪ ማድረጉንም አስታውቋል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበጀት ዓመቱ 39.24 ቢሊዮን ብር ከአዲስ ደንበኞች፣ 2.68 ቢሊዮን ብር ከኪራይና ከተለያዩ ገቢዎች የተሰበሰበ መሆኑንና በአጠቃላይ 118.9 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ተናገሩ፡፡ ይህም በ2017 ዓ.ም. ከነበረበት 63.12 ቢሊዮን ብር አኳያ 88.4 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ተጠቁሟል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ስለገቢውና ወጪው የተናገሩት የ2018 ዓ.ም. በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዶችን በሚመለከት ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ ነው፡፡ የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጌቱ ገረመው (ኢንጂነር) እንደገለጹት፣ 68.01 ቢሊዮን ብር ለኦፕሬሽንና 65.59 ቢሊዮን ብር ደግሞ ለካፒታል ፕሮጀክቶች በበጀት ዓመቱ ወጪ ተደርጓል፡፡ በአጠቃላይ ወጪው 133.6 ቢሊዮን ብር መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ከወጪዎች ውስጥ ዕቃ ግዥና ጥገና ከፍተኛውን ድርሻ ማለትም 55.21 ቢሊዮን ብር የሚይዝ ሲሆን ለኃይል ግዥ ደግሞ 48.42 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉን አስረድተዋል፡፡ ለግብርና ለመንግሥት ገቢ መደረግ የነበረበት 12.39 ቢሊዮን ብር መከፈሉንም ጠቁመዋል፡፡ አገልግሎቱ ወጪ ያደረገውን ገንዘብ ያገኘበትን ምንጭ ሲያብራሩ፣ 107.65 ቢሊዮን ብር ወይም 80.6 በመቶ...
Social-88-1.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-08-10 02:21:26
ፈቃድ መንጠቅን ጨምሮ እስከ 100 ሺሕ ብር ድረስ ቅጣት ይጣላል ተብሏል የመጠቀሚያ ፈቃድ ሳይኖራቸው ጅምር ሕንፃዎችን ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚያውሉ የመንግሥትም ሆነ የግል ድርጅቶችና ግለሰቦችን ከማስጠንቀቂያ ያለፈና ፈቃድ እስከ መንጠቅ የሚያደርስ ቅጣት መቅጣት ሊጀመር መሆኑን፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ገለጸ፡፡ ኮሚሽኑ የቅጣት ዕርምጃ እንደሚወሰድ ያስታወቀው፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሊከሰቱ የሚችሉ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ አደጋዎችን አስቀድሞ በመከላከል የነዋሪዎችን ሕይወት፣ ንብረትና የልማት አውታሮች ለመጠበቅ የወጣውን የአደጋ ሥጋት ደኅንነት ደንብ ቁጥር 132/2014 ማስፈጸም የሚያስችለውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአደጋ መከላከል፣ ቁጥጥር፣ ፍተሻና ብቃት ማረጋገጥ ሥርዓት መመርያ ቁጥር 163/2017 እንዲያስተገብር፣ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ውክልና ሲሰጥ ነው። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈጻሚ አካላትን እንደገና ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 86/2016 አንቀጽ 16 (15) መሠረት፣ ለሥራ ቅልጥፍና ሲባል ውክልና የተሰጠው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ፣ በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ የሚገኝ ማንኛውም ግለሰብ፣ መንግሥታዊም ሆነ የግል ድርጅት...
Fadavers.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-08-09 17:20:12
የዲጂታል መታወቂያ 6.6 ቢሊዮን ዶላር ቀጥታ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ያስገኛል ተብሏል በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥር እንደ አንድ ንግድ ተቋም በመንግሥት የልማት ድርጅትነት እንደገና የተደራጀው ፋይዳቨርስ፣ ወደፊት ገቢ ከሚያመነጭባቸው ዋና ዋና የሥራ መስኮች መካከል፣ ለባንኮችና ለሌሎች ተቋማት የደንበኞችን ማንነት በኤሌክትሮኒክ የማረጋገጥ (e-KYC) አገልግሎቶች እንደሚገኙበት ተገለጸ። ተቋሙ ለሪፖርተር በሰጠው ማብራሪያ፣ ፋይዳቨርስ ገቢ የሚያመነጨው በባንኮችና በተለያዩ ተቋማት የደንበኛ ማንነትን በኤሌክትሮኒክስ በማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ የትምህርት ማስረጃዎች፣ የመንጃ ፈቃዶች፣ ከዲጂታል የይዞታ ማረጋገጫ ሰነዶችና ሌሎች መንግሥታዊ ሰነዶችን በዲጂታል ክሬደንሽያል መልክ በማቅረብ፣ በማረጋገጥና በማሻሻል በሚሰጠው የአገልግሎት ክፍሉና በተጨማሪም በዲጂታል ዋሌት ሥርዓትም በኩል ይሆናል ተብሏል። በተጨማሪም ፋይዳቨርስ ከአገር ውስጥ ባለፈ በሌሎች አገሮች የዲጂታል ሕዝባዊ መሠረተ ልማት (DPI) እና የዲጂታል ሕዝባዊ ሀብቶች (DPG) ዘርፍ የቴክኖሎጂ አቅርቦት፣ የማማከርና የቴክኒክ ድጋፍ አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተገልጿል። የፋይዳቨርስ ምሥረታ ይፋ በተደረገበት ወቅት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ ተቋሙ እ.ኤ.አ. 2030 ድረስ የአገሪቱን አጠቃላይ የአገር ውስጥ ጥቅል ምርት (GDP) በስድስት በመቶ ያሳድጋል፣ በቢሊዮን የሚቆጠር ገቢም ያስገኛል ብለዋል፡፡ ይህንን አስመልክቶ ሪፖርተር ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ማብራሪያ የጠየቀ ሲሆን፣...
Honelign.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-08-09 17:19:07
የፌዴሬሽን ምክር ቤት አንድ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመፍጠር የሚያግዙ የፍትሐ ብሔር ጉዳዮችን የመለየት፣ ረቂቅ ሕጎችን አዘጋጅቶ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የማቅረብ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንዳልሆነ በጥናት ተመላከተ፡፡ ይህ የተገለጸው የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በ2018 በጀት ዓመት ካከናወናቸው አምስት ጥናቶች አንዱ በሆነው፣ አንድ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመገንባት የሚያስችል የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች የሕግ አወጣጥ በኢትዮጵያ ጥናት ግኝት ነው፡፡ ጥናቱን ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ኢንስቲትዩቱ ባዘጋጀው የማፀደቂያ ዓውደ ጥናት ላይ ያቀረቡት፣ የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት ዲን አቶ ሆነልኝ ኃይሉ የተጣጣሙ የኢንቨስትመንት፣ የገበያና የአሠሪና ሠራተኛ ሕግጋትና ወጥነት ያላቸው የንግድ ሕግጋት አንድ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመመሥረት አስፈላጊ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የፌዴሬሽ ምክር ቤት አንድ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመፍጠር በሚያስችሉ የፍትሐ ብሔር ጉዳዮች ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕግ ሊወጣባቸው የሚገቡ የፍትሐ ብሔር ጉዳዮችን የመለየት ሥልጣንና ኃላፊነት፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 55 እና 62 እንደተሰጠው ተጠቅሷል፡፡ ሆኖም አንድ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመፍጠር የሚያግዙ የፍትሐ ብሔር ጉዳዮችን የመለየት፣ የማነሳሳትና ረቂቅ ሕግ አዘጋጅቶ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የማቅረብ ሕጋዊ ሥልጣን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት...
Justic-2.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-08-09 09:08:21
የሥርዓት ለውጥ ከተደረገበት 2010 እስከ 2018 ዓ.ም. የወጡ አብዛኛዎቹ አዋጆች በችኮላና በይድረስ ይድረስ የተዘጋጁ በመሆናቸው፣ ለተደጋጋሚ ማሻሻያዎች መጋለጣቸውንና የአዋጁን ድንጋጌ የጣሱ ደንብና መመርያ እንዲወጡ ምክንያት መሆናቸውን የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር ባጠናው ጥናት አስታወቀ፡፡ ኢንስቲትዩቱ ስለተደረገው ጥናት ያስታወቀው፣ የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር በ2018 ዓ.ም. ያከናወናቸውን አምስት ጥናቶች ማፀደቂያ ዓውደ ጥናት ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ሲካሄድ ነው፡፡ የሕግ አወጣጥ ሥርዓት መረጋጋት በኢትዮጵያ በሚል ኢንስቲትዩቱ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር ያደረገው ጥናት ግኝት፣ በ2010 ዓ.ም. የተደረገውን አገራዊ ለውጥ ተከትሎ የወጡ አብዛኞቹ አዋጆች በችኮላና በይድረስ ይድረስ የተዘጋጁ ስለነበሩ ለተደጋጋሚ ማሻሻያዎች የተጋለጡ መሆናቸውን ጥናቱን ያቀረቡት የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር ሙሐመድ ዳውድ (ረዳት ፕሮፌሰር) ገልጸዋል፡፡ ከ2010 እስከ 2018 ዓ.ም. ድረስ ባሉት ዓመታት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወጡ ሁሉም አዋጆች በጥናቱ መሸፈናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ የሕግ አወጣጥ ሥርዓት መረጋጋትን በተመለከተ አገሪቱ ምንም ዓይነት ፖሊሲ የላትም ተብሏል፡፡ ለአብነትም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን እንደገና ለማቋቋም የወጣ አዋጅ ቁጥር 1115/2011...
Corruption.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-08-09 09:07:09
ለሙስና ጠቋሚዎች (Whistleblowers) ደኅንነት ዋስትና የሚሰጥ የተጠናከረና አፋጣኝ የጥበቃ ሥርዓት እንዲኖር፣ የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ባወጣው ጥናት ጠየቀ፡፡ በመንግሥትና በሌሎች አገልግሎቶች ሰጪ ተቋማት ውስጥ የሙስና አዝማሚያ ወይም ድርጊት መኖሩን የሚጠቁሙ አካላትን የደኅንነት ጥበቃ በሚመለከት፣ የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በሟቋሚያ አዋጁ 1236/2021 በግልጽ ተደንግጓል፡፡   በአዋጁ ሙስናን ለመከላከል ለኮሚሽኑ ጥቆማ በመስጠታቸው ምክንያት በተጠቆበት ወገን የቂም በቀል ዕርምጃ ሊወሰድባቸው የሚችሉ ጠቋሚዎች ሲኖሩ፣ ተገቢውን ማጣራት በማድረግ ጥበቃ እንደሚደርግላቸው ተደንግጓል፡፡ አዋጁ ይህን ቢልም በተደነገገው ልክ ለጠቋሚዎች የሚሰጠው ከለላ እምብዛም መሆኑን፣ የኮሚሽኑ ባለሙያዎች በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲናገሩ ይደመጣል፡፡ ለኮሚሽኑ አራተኛ የሆነው ብሔራዊ የሙስና ዳሰሳ ጥናት ሰነድ እንደሚያሳየው፣ የጥናቱ ተሳታፊዎች ሙስና አሳሳቢ ችግር መሆኑንና አሁን ያለው የሙስና ደረጃ ከአምስት ዓመት በፊት ከነበረው ምጣኔ የበለጠ ስለመሆኑ በመረጃ ሰጪዎች በብዛት የተነገረ መሆኑን ያብራራል፡፡ ጥናቱ ተቋማዊ ሪፎርምና ከፍተኛ ተጠያቂነትን ሊያመጡ የሚችሉ ዕርምጃዎችን በመተግበር የሕዝቡን እምነት መመለስ እንደሚያስፈልግ ያስረዳል፡፡ ሪፖርተር የተመለከተው የኮሚሽኑ የዳሰሳ ጥናት እንደሚያሳየው፣ የጥቆማ ሒደቱ የተንዛዛ መሆን፣ ዜጎች እንዴት መጠቆም እንዳለባቸው መረጃ አለመኖር፣ ጥቆማ አቅራቢዎች...
AFDB.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-08-09 01:35:13
የዲጂታል የታክስ አስተዳደርንና ሌሎች ዕርምጃዎችን ማስፋፋትን እንደ መፍትሔ አስቀምጧል የአፍሪካ ልማት ባንክ እ.ኤ.አ. የ2026 የምሥራቅ አፍሪካ ኢኮኖሚ ትንበያ ሪፖርት ላይ እንደገለጸው የኢትዮጵያ፣ የሶማሊያ፣ የሱዳን፣ የኬንያ፣ የታንዛኒያ፣ የኡጋንዳና ሩዋንዳ የውጭ ዕዳ ከፍ ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ጠቅላላ የውጭ ዕዳ ከጥቅል አገራዊ ምርት አንፃር እ.ኤ.አ. በ2025 ወደ 33.9 በመቶ ከፍ ማለቱን በሪፖርቱ ጠቁሟል፡፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ ከቀናት በፊት ያወጣው እ.ኤ.አ የ2026 የምሥራቅ አፍሪካ ኢኮኖሚ ትንበያ ሪፖርት፣ የኢትዮጵያንና የቀጣናውን አገሮች የዕዳ ጫና ከጥቅል አገራዊ ምርት አንፃር፣ የዕዳ አከፋፈል ሁኔታ፣ ለመዋቅራዊ ለውጥ የሚያስፈልገው ፋይናንስ ሊያጋጥሙ ይችላሉ ስላላቸው የበጀት ክፍተቶች፣ በሕገወጥ የፋይናንስ ፍሰት ስላጋጠመ ኪሳራ፣ በጀትን በኃላፊነት ጥቅም ላይ የማዋልና ይህንንም ግልጽ ማድረግን ደረጃን ጨምሮ ሌሎችም በርካታ አመልካቾችን  ይዟል። ሰነዱ የምሥራቅ አፍሪካን የዕዳ እንቅስቃሴ ሁኔታና በልማት ፋይናንስ ላይ ያለውን ተፅዕኖ በተመለከተ ዝርዝር መረጃ የተነተነበት ክፍል እንደሚገልጸው፣ የኢትዮጵያ ጠቅላላ የውጭ ዕዳ ከጥቅል አገራዊ ምርት (GDP) አንፃር ሲታይ እ.ኤ.አ በ2024 ከነበረበት 23.8 በመቶ በተከታዩ 2025 ዓመት ወደ 33.8 በመቶ ከፍ ማለቱን አመልክቷል። በሪፖርቱ የቀረበው መረጃ የሚያሳየው ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ...
TTelemt.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-08-09 01:34:10
በድርቁ 14 ሺሕ የቁም እንስሳት ሞተዋል ተብሏል ‹‹ጉዳቱን የሚያጠና ግብረ ኃይል አቋቁመን ወደ አካባቢው ልከናል›› የሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር ‎በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በሚገኙ አሥር ቀበሌዎች በተከሰተ ድርቅ 3,386 ነዋሪዎች ወደ አጎራባች ወረዳዎች መፈናቀላቸውን የጠለምት ወረዳ አስታወቀ፡፡ ‎ከሚያዝያ ወር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በወረዳው በሚገኙ 24 ቀበሌዎች ውስጥ በአሥሩ ዝናብ ባለመጣሉ 3,386 ነዋሪዎች ቀዬአቸውን ለቀው መሰደዳቸውንና 14,089 የቁም እንስሳት መሞታቸውን፣ የጠለምት ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዳነ እሸቴ ለሪፖርተር ተናግረዋል። ‎እርን፣ በተል፣ በስቅያ፣ መረው ብላ፣ መረው ገብርኤል፣ አገጣ፣ ደረባ፣ ከረዋ፣ ነጋዴ መሻገሪያና አተባ የተባሉ ቀበሌዎች፣ እስካሁን ምንም ዝናብ ያላገኙ መሆናቸውን የጠቀሱት አቶ አዳነ፣ ሌሎች ስድስት ቀበሌዎች ደግሞ ከሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ዝቅተኛ የዝናብ መጠን እያገኙ መሆናቸውንና ቀሪዎቹ ስምንት ወረዳዎች ዝናብ እያገኙ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ‎የሰሜን ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ክቡር አሰፋ በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ከፍተኛ የዝናብ እጥረት መኖሩን ገልጸዋል። በጠለምት ወረዳ ብቻ ሳይሆን በዞኑ በተለያዩ ወረዳዎች ድርቅ ያጋጠመ ቢሆንም፣ ከሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በኋላ...
Translate »