Etiópia

Ethiopian-Reporter-social-media.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-07-20 12:09:07
በታደሰ ሻንቆ የሃያኛው ክፍለ ዘመን መባቻን ይዞ እስከ ጣሊያን ወረራ የነበሩ ዘመናዊ ዕውቀትንና ኑሮን የቀመሱ ለውጥ ፈላጊዎች ለዛሬም የሚናፈቅ አርዓያነት አላቸው፡፡ በዚያን ጊዜ በተለያየ አጋጣሚ ወደ ፈረንጅ አገር ሄዶ ለመማር፣ አጭር ጉብኝት ለማድረግ ዕድል የገጠማቸው ወይም ከአገራቸው ሳይወጡ በትምህርት ቤት በኩልና በራሳቸው የንባብ ጥረት አዲስ ዕውቀትን የተቋደሱ ልሂቃን የራሳቸውን ህሊና በማላቅ የሚረኩ አልነበሩም፡፡ የሕዝብ አስተሳሰብን፣ ኑሮን ለመለወጥ፣ አገርን ለማሻሻል ሲሉ ያላቸውን ዕውቀት በጋዜጣና በመጻሕፍት ሕዝብ ዘንድ ለማድረስ ይጣጣሩ ነበር፡፡ አዲስ ያገኙት የዘመናዊ አኗኗር ግንዛቤ ሕዝብ ውስጥ እንዲሰርፅ ይጥሩ እንደ ነበር ሁሉ፣ ነባሩንና የጥንቱን ሥርዓተ ኑሮ እንደ ዋዛ ሳይረሳ ለመጪው ትውልድ ለማቆየት፣ ኃላፊነትን ለራሳቸው የሰጡም ነበሩ፡፡ ከእነ መላኩ በጎ ሰው፣ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ፣ ተክለ ሐዋሪያት ተክለ ማርያም፣ ማኅተመ ሥላሴ ወልደ መስቀልና መርስዔ ሐዘን ወልደ ቂርቆስ ዘመን አንስተን እስከ እነ ከበደ ሚካኤልና ተክለፃድቅ መኩሪያ ድረስ ስንጓዝ የምናገኘውን ባወቁት ነገር አገርን ለመጥቀም የነበረውን ጥረት ከዛሬ ቸለልታ ጋር ስናነፃፅረው አንድ ነገር እንደ ጎደለ ይሰማናል፡፡ ብዙ ችግሮችና ምክንያቶች መደርደር ቢቻልም ትልቁ ችግር አውቆ ልቆ ለወገን/ለአገር...
Politics-3.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-20 12:06:45
በኢትዮጵያ የአሜሪካው አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ከአዲስ አበባ መቀሌ ድረስ ተጉዘው ቢመለሱም፣ ከሕወሓት መሪ ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ጋር አልተገናኙም መባሉ ብዙዎችን ያስገረመ ነበር፡፡ ይሁንና አምባሳደሩ መቀሌ ድረስ ሄደውም የጊዜያዊ አስተዳደሩን ፕሬዚዳንት ሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደን በአካል ሳያገኙ በስልክ ብቻ አውርተው ተመለሱ መባሉ ደግሞ የበለጠ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ አምባሳደሩ ኤርፖርት ሲደርሱ የኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አብረሃም ሐጎስ (ዶ/ር)፣ እንዲሁም የሕወሓት ሥራ አስፈጻሚ አባል አዲስ ዓለም ባሌማ (ዶ/ር) ብቻ ናቸው አቀባበል ያደረጉላቸው መባሉም ጥያቄ የፈጠረ ጉዳይ ነበር፡፡ በመቀሌ ቆይታቸውም የሕወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ አማኑኤል አሰፋን ብቻ ተገናኝተው መመለሳቸው በሰፊው የተነገረ ሲሆን፣ የሕወሓትም ሆነ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ቁንጮ አመራሮች እንደ ከዚህ ቀደሙ ያላገኙዋቸው አንዳች መልዕክት ከበስተጀርባው ያዘለ ክስተት ነው የሚል ግምት አሳድሯል፡፡ የአሜሪካ ኤምባሲ በኦፊሴላዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾቹ ላይ ስለአምባሳደሩ ጉዞ በሰጠው አጭር መረጃ ማሲንጋ ከትግራይ ‹‹የፖለቲካና የሲቪክ ማኅበራት አመራሮች›› ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን የጠቆመ ቢሆንም፣ ከሕወሓትም ሆነ በሕወሓት በኃይል እንዲፈርስ ተደረገ ከሚባለው ከሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ ጊዜያዊ አስተዳደር ቁንጮ ባለሥልጣናት ጋር ስለመገናኘታቸውም ሆነ ስለመነጋገራቸው ያለው...
Diyaspora.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-07-20 03:27:35
ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በመካሄድ ላይ ባለው አገራዊ ምክክር ጉባዔ፣ ከአንድ መቶ በላይ የዳያስፖራ አባላት እየተሳተፉ መሆናቸውን የዳያስፖራ አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ ይህን ያስታወቀው ፒፕል ቱ ፒፕል (People to People) 25ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን አስመልክቶ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. በስካይ ላይት ሆቴል ባዘጋጀው የዕውቅና መርሐ ግብር ላይ ነው፡፡ የዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ፍፁም አረጋ (አምባሳደር) እንደተናገሩት፣ እየተካሄደ በሚገኘው አገራዊ የምክክር ጉባዔ በምርጫ የተወከሉ 91 የዳያስፖራ አባላት በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡ በተጨማሪም ከአሁን በፊት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በኢንቨስትመንትና በሌሎች የሥራ መስኮች ተሰማርተው የሚገኙ 12 ዳያስፖራዎችም፣ በምክክር ጉባዔው ተሳታፊ ሆነዋል ብለዋል፡፡ በአጠቃላይ ከአንድ መቶ በላይ የዳያስፖራ አባላት በውጭ አገር የሚኖረውን የዳያስፖራ ማኅበረሰብ በመወከል በአገራዊ የምክክር ጉባዔ እየተሳተፉ ናቸው ያሉት አረጋ (አምባሳደሩ)፣ ‹‹የምንገኝበት የክረምት ወቅት በርካታ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የልጆቻቸው ትምህርት ቤት በመዘጋቱ የሥራ ጊዜያቸውን በማመቻቸት ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡበት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ቆይታቸውም ቤተሰብ ከመጠየቅና አገር ከመጎብኘት ባለፈ፣ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች በመሳተፍ ማኅበረሰቡን የሚጠቅም ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ይሰጣሉ፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡   ፍፁም...
AFDP.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-20 03:26:26
የአፍሪካ ልማት ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ለሆነውና ሲጠናቀቅ 300 ሜጋ ዋት ኃይል ለሚያመነጨው የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት፣ 110 ሚሊዮን ዶላር ብድር ማፅደቁን አስታወቀ፡፡ የባንኩ የዳሬክተሮች ቦርድ ብድሩን ያፀደቀው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ለኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ ወሳኝ የመሸጋገሪያ ምዕራፍ ነው ብሏል፡፡ የፕሮጀክቱ ግምታዊ ወጪ 508 ሚሊዮን ዶላር መሆኑን የገለጸው ባንኩ፣ ካፀደቀው 110 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ ብድር ውስጥ እስከ 80 ሚሊዮን ዶላር የሚደርሰውን ከአፍሪካ ልማት ባንክ የብድር መስጫ ሥርዓት (ADB Window)፣ 20 ሚሊዮን ዶላር ከታዳሽ ቴክኖሎጂ ፈንድ፣ እንዲሁም አሥር ሚሊዮን ዶላር ከአፍሪካ ዘላቂ ኃይል ፈንድ የተውጣጣ የብድር ጥቅል መሆኑን ገልጿል፡፡ በተጨማሪም የ381.1 ሚሊዮን ዶላር የብድር ጥቅል ከሌሎች የልማት ፋይናንስ ተቋማት በማሰባሰብ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ የፕሮጀክቱ ግንባታ የሚካሄደው አሚያ (AMEA) በተሰኘው የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ ኩባንያ ሲሆን፣ ኩባንያው በገባው ውል መሠረት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ለ25 ዓመታት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሽያጭ የሚያቀርብ መሆኑ ይታወቃል፡፡ የፕሮጀክቱ ውል የዲዛይን፣ የግንባታ፣ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን፣ እንዲሁም የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ የአምስት ኪሎ...
Selamawit.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-07-19 18:17:31
በተጭበረበረ ሰነድ የፖስፖርትና ሌሎች የጉዞ አገልግሎቶች ፈላጊዎች ቁጥር ጨምሯል ተብሏል አዲሱን የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት በውጭ አገሮች ለሚገኙ ዜጎች በቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች በኩል ከሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ መስጠት እንደሚጀምር፣ የኢሚግሬሽን ዜግነት አገልግሎት ገለጸ፡፡ አገልግሎቱ ይህን ያስታወቀው የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸሙን በተመለከተ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. በሰጠው መግለጫ ነው። መግለጫውን የሰጡት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር (ወ/ሮ) ሰላማዊት ዳዊት፣ ተቋሙ አዲሱን የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት በአገር ውስጥ በአዲስ አበባ ከዋና መሥሪያ ቤት ጀምሮ በክልሎች በሚገኙ 23 ቅርንጫፎቹ፣ እንዲሁም በ14 የመሶብ አንድ መስኮት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። ይህንን አገልግሎት በተለያዩ የውጭ አገሮች ለሚኖሩ ዜጎች ለመስጠት ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን፣ ከሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ደግሞ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች በሚገኙባቸው የውጭ አገሮች መሰጠት እንደሚጀመር አስታውቀዋል። በእነዚህ አገሮች የሚገኙ ዜጎች የተቋሙ አዲሱን ድረ ገጽ (www.immigration.gov.et) በመጠቀም የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ ብለዋል። በመሆኑም ቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች ባሉባቸው የውጭ አገሮች የሚገኙና የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት የሚፈልጉ ዜጎች በአዲሱ የተቋሙ ድረ ገጽ በማመልከት አገልግሎቱን ማግኘት...
Simegn.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-19 18:15:10
የመረጃ ነፃነት አዋጅን የሚያስፈጽው የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ፓርላማ ገብተው እንዳይዘግቡ የተከለከሉ ሚዲያዎችን በሚመለከት፣ ተጠሪነቱ ለፓርላማው በመሆኑ ፓርላማውን የመቆጣጠር ሥልጣን እንደሌለው ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የመረጃ ነፃነት አዋጅ ቁጥር 1427/2018ን በሚመለከት ዓርብ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ ዋና ዕንባ ጠባቂዋ ወ/ሮ ስመኝ ውቤ መግለጫውን በጽሑፍ ባነበቡበት ወቅት፣ አዋጁ በፓርላማ የፀደቀበትን ዕለት ጨምሮ የግል መገናኛ ብዙኃን በፓርላማ ተገኝተው እንዳይዘግቡ መከልከሉን አስመልክቶ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ምን እየሠራ እንደሆነ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል፡፡ ለጥያቄው ምላሽ የሰጡት ዋና ዕንባ ጠባቂ ወ/ሮ ስመኝ፣ የአዋጁን መፅደቅና ተቋሙ ለፓርላማ ያቀረበውን የ11 ወራት ሪፖርት በርካታ ሚዲያዎች ሲዘግቡ መመልከታቸውን ገልጸው፣ ‹‹ተጠሪነታችን ለፓርላማ ስለሆነ ፓርላማውን ወደ ላይ መቆጣጠር ሥልጣን የለንም፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹ክፍተቱ የት ጋ እንደሆነ እርግጠኛ አይደለንም፤›› ያሉት ዋና ዕንባ ጠባቂዋ፣ ችግር ካለም ምላሽ የሚሰጠው ፓርላማው እንጂ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ምላሽ ለመስጠት እንደሚቸገር ገልጸዋል፡፡ የተሻሻለውን የመረጃ ነፃነት አዋጅ ለማስፈጸም ዕንባ ጠባቂ ሙሉ ሥልጣን የተሰጠው ሲሆን፣ መረጃ በማይሰጡ ኃላፊዎች ላይ አስተዳደራዊ ዕርምጃ የመውሰድና ሥልታዊ ምርመራ የማድረግ መብት...
Politics-22.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-07-19 09:12:13
የመስኖና ቆላማ ሚኒስቴር የፌዴራሉ ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በወልመልና ጨልጨል የመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ ሰፋ ያሉ የኦዲት ግኝቶችን የያዘ ሪፖርት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ፣ የተጀመረውን ስኬታማ ጉዞ ለማደናቀፍና ለማጠልሸት የሚከናወኑ ሥራዎች በፍፁም ተቀባይነት አይኖራቸውም አለ። በተመሳሳይ በፕሮጀክቶቹ ተቋራጭ ሆኖ እየሠራ ያለውና በዋና ኦዲተር የክዋኔ ኦዲት ግኝቶች ላይ ስሙ የተጠቀሰው ዓለማየሁ ከተማ ጠቅላላ ተቋራጭ፣ ዋና ኦዲተር ይፋ ያደረገውን የክዋኔ ኦዲት ግኝቶች ሙሉውን ሪፖርት እንዳልተሰጠው ጠቁሞ፣ የኦዲት ግኝት ተብሎ በመገናኛ ብዙኃን የተገለጸው ሪፖርት እሱን (ተቋራጩን) የማይወክልና ትክክል ያልሆነ ነው ብሏል፡፡ ሚኒስቴሩ ሐምኬ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ የኮንትራትና የፕሮጀክት አስተዳደር ሥርዓትን በአግባቡ መረዳት ያቃታቸው ወይም መንግሥት የግብርና ክፍለ ኢኮኖሚውን አስተማማኝ ወደ ሆነው የመስኖ ምርታማነት ለመቀየር እያደረገ ያለውን ጥረት ለማደናቀፍና ለማጠልሸት ሆነ ተብለው የሚሠሩ ሥራዎች መኖራቸውን በመጥቀስ፣ ይህ በፍፁም ተቀባይነት ሊኖረው አይችልም ብሏል፡፡ ‹‹አገራችን በተለያዩ ዘርፎች አስደናቂ የሆኑ ስኬቶችን እያስመዘገበች ትገኛለች፤›› ያለው የሚኒስቴሩ መግለጫ፣ ከዚህ አንፃር እንደ አገር የምናስመዘግባቸው ስኬቶች ለሕዝባችንና ለአጋሮቻችን የሚሰጠው ትርጉም ትልቅ የመሆኑን ያህል ይህ ጅምር እመርታ የማያስደስታቸው፣ በከፍተኛ...
Politics-55.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-19 09:10:57
‹‹ድልድሉ እንዲስተካከል ይደረጋል›› የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን አንድን ማኅበረሰብ ወክለው በአገራዊ ምክክር ጉባዔው ለመሳተፍ የተገኙ ተመካካሪዎች በአንድ ቡድን ውስጥ ተካተው በአንድ አጀንዳ ብቻ እንዲመካከሩ የተደለደሉበት አካሄድ አሳታፊና አካታች ባለመሆኑ እንዲስተካከል ሲሉ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጠየቁ፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ጥያቄ ተገቢ መሆኑን ያረጋገጠው ኮሚሽኑ ‹‹ድልድሉ እንዲስተካከል ይደረጋል›› ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የሥራ አስፈጻሚ አባል ዮሐንስ መኮንን (አርክቴክት)፣ ለአገራዊ ምክክር ጉባዔው ስምንት አጀንዳዎች መቀረፃቸውን፣ በእያንዳንዱ ውስጥ ዝርዝር አጀንዳዎች እንዳሉ ለሪፖርተር ገልጸዋል። ተመካካሪዎች በቴክኖሎጂ ወይም በሰው ሠራሽ አስተውሎት በስምንት ቡድን ውስጥ እንዲደለደሉ መደረጉን፣ ከሞላ ጎደል አካሄዱ ጥሩ ሊመስል ቢችልም ለሁሉም ተመካካሪዎች አሳታፊ አለመሆኑን ተናግረዋል። ከኢዜማ የተወከሉ አራት ተመካካሪዎች መኖራቸውን በምሳሌነት የጠቀሱት ዮሐንስ (አርክቴክት)፣ ሁሉም አንድ አጀንዳን በተመለከተ ለመነጋገር በአንድ ቡድን ውስጥ መደልደላቸውን ተናግረዋል። ይህ የሆነበት የድልደል አካሄድ ተገቢ አይመስለኝም ያሉት ዮሐንስ (አርክቴክት)፣ ተበታትነው በተለያዩ አጀንዳዎች ውስጥ እንዲገቡ ቢደረግ፣ የሌሎችንም ሐሳብ ለማድመጥና እነሱም አለን የሚሉትን ሐሳብ ለማካፈል ዕድል እንደሚሰጣቸው አስረድተዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ፖሊሲና የተደራጀ ሐሳብ እንዳላቸው፣ ከዚህም አንጻር ሁሉንም አንድ አጀንዳን...
Politics-33-1.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-07-18 23:35:53
በአገር ውስጥ መዋዕለ ንዋይ ለሚያፈሱ ባለሀብቶች ምቹ የኢንዱስትሪ ምኅዳር መፍጠር፣ የፋይናንስ አቅርቦት ማመቻቸት፣ የኢንቨስትመንት የመሠረተ ልማት ማነቆዎችን መፍታት ጨምሮ የሚገጥሟችውን ችግሮች በማስተካከል፣ ከውጭ ከሚገቡ ምርቶች ጥገኝነት መላቀቅ እንደሚያስፈልግ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች አሳሰቡ፡፡ ባለሙያዎቹ ይህን የተናገሩት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን 23ኛውን  ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ዓርብ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. ሲያካሂድ ነው፡፡ በመድረኩ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)፣ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብረሃም ንጉሤ፣ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች፣ የተለያዩ ድርጅቶች ተወካዮችን ጨምሮ በርካታ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡ የአሶሴሽኑ ፕሬዚዳንት ጣሰው ወልደሃና (ፕሮፌሰር) የአገሪቱ ኢኮኖሚ በዓለም አቀፍ ደረጃ በነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ምክንያት በተፈጠረ የሸቀጦች የዋጋ ንረት ዝቅተኛ ገቢ ያለቸው ዜጎች የመግዛት አቅም መፈተኑን፣ በውጭ ብድር ጫና መብዛትና የውጭ ምንዛሪ ላይ አለመረጋጋት አለመታየቱ ፈታኝ ጉዳዮች ናቸው ብለዋል፡፡ በአጠቃላይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ገቢ ሳይሻሻል ኢኮኖሚው አደገ መባሉ በቂ አይደለም ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት የመጨረሻ ውጤቱ ምርታማና በየዓመቱ ለሥራ ዝግጁ ለሚሆን ሁለት ሚሊዮን አዲስ የሰው ኃይል የሥራ ዕድል መፍጠር፣ የዜጎች ገቢ መጨመር፣ ድህነት...
Lucy-99.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-18 23:33:15
‹‹በአቡዳቢ የተፈጥሮ ታሪክ ሙዚየም ውስጥ ጎብኚዎች ፍጥነታቸውን የሚቀንሱበት፣ ድምፃቸውን ዝቅ የሚያደርጉበትና ብዙ ጊዜ ፀጥ የሚሉበት አንድ ልዩ ጋለሪ አለ። ከፊታቸው፣ በጥንቃቄ መብራት የበራላትና መጠኗ እጅግ አነስተኛ የሆነችው የ3.2 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ ባለቤት የሆነችው የሆሚኒን አፅም (የቅድመ ሰው ቅሪተ አካል) ሉሲ (ድንቅነሽ) ትገኛለች። ምናልባትም ከማንኛውም ሌላ ጥንታዊ የሰው ዘር ዘመዶቻችን ይልቅ፣ ሉሲ ‹ሰው መሆን ምን ማለት ነው?› የሚለውን ጥያቄ በጥልቀት እንድናስብበት ትገፋፋናለች።›› የሉሲ ቅሪተ አካል በአቡዳቢ የተፈጥሮ ታሪክ ሙዚየም ለዕይታ ቀርቦ – ፎቶ አቡዳቢ የተፈጥሮ ታሪክ ሙዚየም ይህን ኃይለ ቃል ከሁለት ሳምንታት በፊት በዘ ኮንቨርሴሽን (The Conversation) መጽሔት ላይ የጻፉት የአቡዳቢ የተፈጥሮ ታሪክ ሙዚየምና የለንደን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የጄኔቲክስ፣ ዝግመተ ለውጥና አካባቢ ጥናት ክፍል ዳይሬክተር ፒተር ኪዬርጋርድ እንዲሁም በተመሳሳይ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የምድር ሥርዓት ሳይንስ ፕሮፌሰር  የሆኑት ማርክ ማስሊን ናቸው፡፡ ካለፈው ኅዳር ወር ጀምሮ እስከ ሐምሌ መጀመርያ ድረስ ለዘጠኝ ወራት በአዲሱ የአቡዳቢ የተፈጥሮ ታሪክ ሙዚየም ለዕይታ የበቃችው ሉሲ የአቡዳቢ ክራሞቷን አስመልክቶ ሁለቱ ምሁራን ሐተታ አቅርበዋል፡፡ ለመጀመርያ ጊዜ ወደ እስያ አኅጉር ያቀናችው ሉሲ፣ ከዓምና...
Translate »