Etiópia

Sport-4.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-29 09:48:48
አሜሪካ የወንዶች የዓለም ዋንጫን በታሪኳ ስታስተናግድ የዘንድሮው ውድድር ለሁለተኛ ጊዜ ነው።የመጀመሪያዋ  የ1994ቱ  ውድድር ሲሆን  ለብቻዋ ያሰናዳችው በመሆኑ ካሁኑ ይለያል። በወቅቱ በየስታዲየሙ የተመዘገበው ከፍተኛ የተመልካቾች ቁጥር   በፊፋ የዓለም ዋንጫ ታሪክ ሳይሰበር የቆየ ትልቅ ክብረ ወሰን ነበር። በውድድሩም ብራዚል ጣሊያንን በመለያ ምት አሸንፋ ዋንጫውን ማንሳቷ ይታወሳል።በአሜሪካ ለሁለተኛ ጊዜ  እየተካሄደ ያለው 23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ እንደ ቀደመው በአንድ አገር ብቻ ሳይሆን ከጎረቤቶቿ ካናዳና ሜክሲኮ ጋር በመሆን በጋራ እየተከናወነ ይገኛል። የ2026ቱ ውድድር ልዩ የሚያደርጉት ዋና ዋና ነጥቦች አንዱ የቡድኖች ቁጥር ማደግ፣ ይህም ከተለመደው 32 ቡድኖች ወደ 48 ቡድኖች ያደገበት የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ መሆኑ ነው። ሌላው የጨዋታዎች ብዛት ሲሆን አጠቃላይ የጨዋታዎች ብዛት ወደ 104 ከፍ ያለ ብሏል። ከእነዚህ ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ (78 ጨዋታዎችን) የምታስተናግደው አሜሪካ ናት። ይህም ሁሉንም የሩብ ፍፃሜ፣ የግማሽ ፍፃሜና የፍጻሜ ጨዋታን ያጠቃልላል። ቢቢሲ እንደዘገበው፣ የዋይት ሃውስ  የዓለም ዋንጫ ግብረ ኃይል ዋና ዳይሬክተር አንድሪው ጁሊያኒ እንዳሉት፣ አሜሪካ የ2038ቱን የወንዶች የዓለም ዋንጫ ለማስተናገድ ጨረታ ውስጥ ለመግባት ልታስብበት ትችላለች። አሜሪካ የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ከካናዳና ከሜክሲኮ ጋር  እያስተናገደች ያለችው፣ የውድድሩ ቅርፅ  ከ32 ቡድኖች...
Midwife.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-29 03:02:47
30 ሺሕ ሚድዋይፎች ያስፈልጋሉ ተብሏል በኢትዮጵያ በወሊድና ከወሊድ ጋር በተያያዘ ችግር በዓመት ከስምንት ሺሕ በላይ እናቶች እንደሚሞቱ፣ የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማኅበር አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ እንሰርሙ ባዩ፣ ‹‹ኢትዮጵያ የእናቶችን ሞት በከፍተኛ ደረጃ ከቀነሱ የዓለም አገሮች መካከል አንዷ ነች፡፡ አሁን ባለው መረጃ ከ100 ሺሕ ውልደት የእናቶች ሞት ምጣኔ ወደ 141 በመቶ መቀነስ የተቻለ ሲሆን፣ ይህም የዘላቂ የልማት ግብን ለማሳካት እንደ ትልቅ ዕርምጃ የሚወሰድ ነው፤›› ብለዋል፡፡ አቶ እንሰርሙ ባዩ የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማኅበር ፕሬዚዳንት ከሁለትና ከሦስት አሠርት ዓመታት በፊት በወሊድ ምክንያት ከሚሞቱ በሺዎች የሚቆጠሩ እናቶች ቁጥር ጋር ሲነፃፀር በወሊድ በዓመት ውስጥ የሞት ምጣኔው ወደ 141 ዝቅ ማለቱ እንደ ስኬት ቢቆጠርም፣ አሁንም በየዓመቱ ከስምንት ሺሕ በላይ እናቶች ከወሊድ ጋር በተያያዘ ችግር እየሞቱ ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡ በወሊድና ከወሊድ ጋር በተያያዘ ችግር የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር አሁንም ጥቂት የሚባል ባለመሆኑ፣ በዚህ ላይ በርካታ ሥራዎችን መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ 27 ሺሕ ያህል ሚድዋይፎች መኖራቸውን፣ የእናቶች ሞት ቁጥርን አሁን ከሚገኝበት ለመቀነስና እ.ኤ.አ. በ2030 በጤናው ዘርፍ የተያዘውን...
Social-1-2.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-29 03:01:44
የኦስትሪያው  ቴክኒካል  ዩኒቨርሲቲ  ለኢትዮጵያውያን ተማሪዎች  የምህንድስናና የቴክኖሎጂ የድህረ-ምረቃ የትምህርት ዕድሎችን  ለመስጠት ሥምምነት ላይ መድረሱን አስታወቀ፡፡ ስምምነቱ ይፋ የሆነው ረቡዕ ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደው የትብብር መድረክ ላይ ሲሆን፣ በዕለቱ የኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)ና በኢትዮጵያ የኦስትሪያ አምባሳደር ሲሞን ክናፕ (ዶ/ር) በሥፍራው ተገኝተዋል። በትብብር መድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)፣ የፕሮግራሙ መጀመር ኢትዮጵያ አሁን ላይ የማዕድን ዘርፉን በከፍተኛ ፍጥነት ለማሳደግ ለጀመረችው ስትራቴጂ  ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።  ሚኒስትሩ እንደተናገሩት፣ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ እየተስፋፋ ያለውን የማዕድንና የፔትሮኬሚካል ዘርፍ የሚመራ የሠለጠነ የአገር ውስጥ የሰው ኃይል እጥረት በመኖሩ፣ በቡሌ ሆራና በቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲዎች በኩል  ጠንካራ የማዕድን ተቋማትን መገንባት ተጀምሯል። ለዚህም የኦስትሪያ ዩኒቨርሲቲ በተለይ ተስማሚ የሆኑ የትምህርት ዓይነቶችን በመቅረፅና ጥራት ያለው የሰው ኃይል በአጭር ጊዜ ውስጥ በማፍራት በኩል የሚያደርጉት ድጋፍ ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው ጠቁመዋል። የአውሮፓና የኦስትሪያ ዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ ጥራት ያላቸውና በተመጣጣኝ ዋጋ የሚቀርቡ በመሆናቸው፣ ይህንን ዕድል ተጠቅሞ ሒደቱን በፍጥነት ወደ ተግባር በመቀየር የተማሪዎችን አቅም መገንባት እንደሚገባ  አሳስበዋል። በኢትዮጵያ የኦስትሪያ አምባሳደር ሲሞን ክናፕ (ዶ/ር)...
Social-3-1.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-28 20:28:22
በኢትዮጵያ የአርብቶ አደር ማኅበረሰብን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የአየር ንብረት ለውጥ የሚያመጣውን ተፅዕኖ ለመቋቋም፣ የመሬት ይዞታ መብትን በሕግ ማጠናከርና የተቋማትን አቅም መገንባት ተገቢ እንደሆነ የሚያመላክት ጥናታዊ ሰነድ ይፋ ተደረገ። ጥናቱ ይፋ የተደረገው ላንድ ፎር ላይፍ (LfL) ኢትዮጵያ ከብሔራዊ የመሬት ጥምረት ኢትዮጵያ (NLC) ጋር በመተባበር፣ በአርብቶ አደር መሬት ይዞታ፣ በግጦሽ መሬት አስተዳደርና የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም ላይ ያተኮረ የፖሊሲ ውይይት ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ሲደረግ ነው። በተዘጋጀው ውይይት ላይ ጥናታዊ ጹሑፍ ያቀረቡት የፓስቶራሊስት ፎረም ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተዘራ ጌታሁን፣ በአሁኑ ወቅት በምሥራቅ አፍሪካ ከ250 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ሙሉ በሙሉ በእንስሳት ዕርባታ ላይ ተሰማርቷል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ደግሞ ከ12 ሚሊዮን በላይ አርብቶ አደሮች እንደሚኖሩባትና አጠቃላይ የመሬት ስፋት ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነውን የሚሸፍን በመሆኑ፣ ለአገራዊ ኢኮኖሚ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል። እ.ኤ.አ. በ2019 በተደረገ የገበያ ግምት መሠረት በኢትዮጵያ ያለው የአርብቶ አደሮች እንስሳት አጠቃላይ ሀብት 256 ቢሊዮን እንደሚደርስ አቶ ተዘራ በጥናታቸው አስረድተዋል። ሆኖም ይህ ግዙፍ የኢኮኖሚ ዘርፍ በአሁኑ ወቅት የፀጥታ ችግሮች፣ የግጦሽ መሬት መጥበብ፣...
Fantahun.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-28 20:27:10
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየጨመረ በመጣው የነዋሪዎች ቁጥር ምክንያት የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ችግር ሆኖ መቀጠሉ ተገለጸ። ከፍተኛ የማዕድን በተለይም የወርቅ ሀብት እንዳላት በሚነገርላት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ የንፁህ መጠጥ ውኃ አቅርቦት ችግር አሁንም ድረስ መቀጠሉን፣ በክልሉ የውኃና ኢነርጂ ቢሮ የዕቅድ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፈንታሁን ባንቴ ለሪፖርተር ገልጸዋል። ከ3‚500 በላይ የሚሆኑ የውኃ ተቋማት መኖራቸውንና ከእነዚህ ውስጥ በፀጥታ ችግር ምክንያት ከ500 በላይ የሚሆኑት ጉዳት እንደደረሰባቸው፣ አሁንም ድረስ ያልታደሱና አገልግሎት መስጠት ያልጀመሩ የውኃ ተቋማት መኖራቸውን ተናግረዋል። በፀጥታ ችግሩ ወቅት ከ1‚500 በላይ የውኃ ተቋማት ጉዳት ደርሶባቸው እንደነበር የገለጹት አቶ ፈንታሁን፣ አክሽን አጌንስት ሃንገር ኢትዮጵያ (Action Against Hunger) የተሰኘውን የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅትን ጨምሮ፣ ሌሎች ድርጅቶችም ተረባርበው አብዛኞቹ የውኃ ተቋማት የማደስ ሥራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ከ35 እስከ 40 በመቶ የሚሆነው የክልሉ ሕዝብ አሁንም ድረስ ንፅህናውን ያልጠበቀ የወንዝና የኩሬ ውኃ እንደሚጠቀም አስረድተዋል። የክልሉ የሕዝብ ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ መሆኑንና በተለይም በአሁኑ ወቅት ከሌሎች አጎራባች ከተሞች የተሻለ አንፃራዊ ሰላም በመኖሩ ከአራትና አምስት ዓመታት ወዲህ የሕዝብ ቁጥሩ ከፍተኛ...
Getachew.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-28 13:43:24
እንደ ኢትዮጵያ ላሉ የባህር በር ለሌላቸው አገሮች የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ትስስር መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ የምትጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ፡፡ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬት ስትራቴጂ ጥናትና ምርምር ማዕከል፣ እንዲሁም አንዋር ጋርደስ የዲፕሎማቲክ አካዴሚ ከተሰኘ ተቋም ጋር በመሆን ‹ሂሊ ዲያሎግ የተሰኘ› የምክክር መድረክ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡ በውይይቱ የተገኙት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ ባደረጉት ንግግር፣ ኢትዮጵያ ወደብ አልባ አገር በመሆኗ አሳሳቢ ችገሮች እያጋጠሟት መሆኗን ገልጸዋል፡፡ የወደብና የባቡር መስመሮች መተሳሰር ትልቅ ኢንቨስትመንት የሚፈልግ በመሆኑ፣ ይህንን ትስስር እንደ ተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ ያሉ የተሻለ አቅም ያላቸውን አጋሮች ሳያሳትፉ ማከናወን አይቻልም ብለዋል፡፡ በአፍሪካ በትራንስፖርት መተሳሰር፣ የወደቦችን አቅም ማሳደግ፣ የባቡር መስመሮችን መዘርጋት ጨምሮ በሎጂስቲክስ መሠረተ ልማቶች የተሻለ አቅም ያለው አጋር እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስን ጨምሮ ባልተነካው የአፍሪካ ሀብት ላይ መዋዕለ ንዋያቸውን በማፍሰስ ሊሰማሩና የሚታዩ ችግሮችን ሊፈቱ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ በወደብ ልማት ካላት ከፍተኛ...
CEHRO.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-28 13:42:18
በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዕድሜያቸው ለመምረጥ ያልደረሱ ልጆች የመራጭነት ካርድ በመያዝ ቤተሰቦቻቸውን ወክለው ሲመርጡ መታዘቡን፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ኅብረት (ኢሰመድኅ) አስታወቀ፡፡ ኅብረቱ ይህንን ያለው፣ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደውን ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫና ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. በልዩ ጣቢያዎች የተካሄደውን የድምፅ መስጠት ሒደት ትዝብት አስመልክቶ ባወጣው የግኝት ሪፖርት ነው። ዕድሜያቸው ለመምረጥ ያልደረሱ ልጆች የመራጭነት ካርድ በመያዝ ቤተሰቦቻቸውን ወክለው እንዲመርጡ መደረጋቸውን፣ ለልጆቹም የምርጫ አስፈጻሚዎች በድምፅ መስጫ ወረቀቱ ላይ ምልክት ሲያደርጉ መታዘቡን ኅብረቱ ገልጿል። የምርጫ አስፈጻሚዎች በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች በመራጮች የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ላይ ምልክት ሲያደርጉ መስተዋላቸውንም ኅብረቱ በግኝቱ አካቷል። ምርጫ ጣቢያ ውስጥ እንዲገቡ የማይፈቀድላቸው ግለሰቦች (የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ ታዛቢዎችና መራጮች ያልሆኑ ግለሰቦች) በምርጫ ጣቢያው ውስጥ በመገኘት፣ መራጮች ድምፅ እንዴት መስጠት እንዳለባቸው መመርያ መስጠታቸውን፣ ከመራጮች ጋር በሚስጥር ድምፅ መስጫ ቦታ ላይ መገኘታቸውን፣ ይህም ሲሆን የምርጫ አስፈጻሚዎች ተገቢውን ዕርምጃ አለመውሰዳቸውን መታዘቡን ገልጿል። የምርጫ ታዛቢዎችና የፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎች የድምፅ ቆጠራ ሲያካሂዱና ዋጋ ያላቸውና የሌላቸው ድምፆችን ሲለዩ መስተዋላቸው መታዘቡን ኅብረቱ በሪፖርቱ አካቷል።...
Government.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-28 07:02:02
ግንኙነቱ በኢመደበኛ መንገድ እየተመራ መሆኑ ተገልጿል የክልል መንግሥታት ግንኙነት የሚመራበት አዋጅ ከወጣ አምስት ዓመታት ቢሆነውም፣ ግንኙነቱ በኢመደበኛ መንገድ እየተመራ አዋጁ ግን ተግባራዊ አለመደረጉን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት በጥናቱ ማረጋገጡን አስታወቀ፡፡ ‹‹የመንግሥታት ግንኙነት ተስፋዎች፣ መሰናክሎችና መፍትሔዎች›› በሚል ርዕስ ሰሞኑን ባካሄደው ውይይት፣ በኢትዮጵያ የመንግሥታት ግንኑነትን በተመለከተ የተደነገጉ ሕጎችና የፖሊሲ ማዕቀፎች፣ እንዲሁም የተቋማት አደረጃጀት መተግበር አለመቻሉንና ይህም ለግንኙነቱ ዋነኛ መሰናክል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔን፣ የሰላም ሚኒስቴርና ሌሎች ተወካዮችን ጨምሮ በመድረኩ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ተመራማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡ የመንግሥታት ግንኙነትን በተመለከተ ጥናት ያቀረቡት ንጉሤ አፌሻ (ዶ/ር)፣ እ.ኤ.አ. በ2021 የመንግሥት ግንኙነትን ለመምራት የወጣው አዋጅና ሌሎች የክልሎቹን ግንኙነት ሕጋዊ ለማድረግ የወጡ ድንጋጌዎች ባለፉት አምስት ዓመታት መተግበር ባለመቻሉ፣ ወይም ባለበት በመቆሙ ግንኙነቱ ኢመደበኛ በሆነ መንገድ እየተመራ ነው ብለዋል፡፡ የክልሎችን ግንኙነት በአገር አቀፍ ደረጃ ለመምራት ቴክኒካዊና ሙያዊ ድጋፍ ለመስጠት ታስቦ የተቋቋመው አገራዊ የመንግሥታት ግንኙነት ሴክሬታሪያት በሥራ ላይ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ምክንያት የክልል መንግሥታት ግንኙነትን የተመለከቱ የፖሊሲ ሪፎርሞችና ውይይቶች፣ እንዲሁም ቅንጅታዊ ተግባራት በሕጉ መሠረት መካሄዳቸው ቀርቶ...
Politics-6.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-28 07:00:42
የሰላምና ፀጥታ ችግር፣ የመሥሪያ ቦታ እጥረት፣ የግብር ማሻሻያ ተዕፅኖዎች፣ የጉምሩክ ጉዳዮችና የፋይናንስ አቅርቦት አናሳ መሆን፣ ለግሉ ዘርፍ ዋነኛ ማነቆዎች ሆነው መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኀበራት ምክር ቤት ጥናት አመላከተ፡፡ የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኀበራት ምክር ቤት ከሳይፕ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር፣ ሦስተኛውን ብሔራዊ የቢዝነስ አጀንዳዎች የባለድርሻ አካላት የማሳወቂያና ተጨማሪ ግብዓት የማሳወቂያ ዓውደ ጥናት ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ተካሂዷል። በዓውደ ጥናቱ የግሉ ንግድ ዘርፍ ማነቆ የሆኑ ጉዳዮች በጥናት ተለይተው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል። የኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኀበራት ምክር ቤት የጥናትና አድቮኬሲ ተጠባባቂ ዳይሬከተር አቶ ታከለ አየለ፣ ሦስተኛውን ብሔራዊ የቢዝነስ አጀንዳ አስመልክቶ ባቀረቡት የጥናት ሰነድ በሕጋዊ፣ በመዋቅራዊና በአስተዳደራዊ ማነቆዎች ምክንያት የግሉ ዘርፍ በአገር ደረጃ ባለው አቅም እየተንቀሳቀሰ አይደለም ብለዋል። ብሔራዊ የንግድ አጀንዳ በዘርፉ ያሉ ዋና ዋና ችግሮችን በመለየትና ጥልቅ ጥናቶችን በማድረግ በሚመለከተው የመንግሥት አካል እንዲፈቱ ግፊት ለማድረግ ነው በማለት፣ የ569 ኢንተርፕራይዞች ሐሳብ የተካተተበት ጥናት ተደርጎ ከአሥር የሚበልጡና ለግሉ ዘርፍ ማነቆ የተባሉ ቁልፍ አጀንዳዎች መለየታቸውን ተናግረዋል። በዚህም መሠረት 59.6 በመቶ የጥናቱ ተሳታፊዎች ከግብር ማሻሻያና ከጉምሩክ...
Parlama-2.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-28 00:19:27
በመረጃ ነፃነት አዋጅ ሙስናን ወይም ሌላ ሕገወጥ አሠራርን፣ የሥራ አፈጻጸም ብቃት ጉድለትን ወይም የግለሰብ ወይም የመንግሥት አካል ወይም የድርጅት ሕገወጥነት ለመሸፈን፣ መረጃና ሰነድ በሚስጥር እንዲያዝ ያደረገ ኃላፊ አምስት ዓመት እንዲቀጣ የሚያደርግ አዋጅ ፀደቀ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመንግሥትና የግል ድርጅቶች በእጃቸው ያለን መረጃ እንዲሰጡ የሚያስገድደውን የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ በተመለከተ ያቀረበው ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ፣ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቋል፡፡   ፓርላማው መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው 14ኛ መደበኛ ስብሰባ የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ ላይ የመጀመሪያ ንባብ አካሂዶ፣ ረቂቅ አዋጁን ለዝርዝር ዕይታ ለዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መመራቱ ይታወሳል፡፡ ከሁለት ወራት ውይይት በኋላ የቀረበው የውሳኔ ሐሳብ እንደሚያብራራው፣ የወንጀል ጥፋቱ በፍርድ የተረጋገጠበት የበላይ ኃላፊ፣ የመረጃ ኃላፊ ወይም ይህንን ያዘዘ ሌላ ኃላፊ ከአምስት ዓመት በማይበልጥ እስራት ወይም በመቶ ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ ደንግጓል፡፡ በተመረጡ አንዳንድ ተወዳጅና የመንግሥት ሚዲያዎች ብቻ በተጋበዙበት የምክር ቤቱ መደበኛ ጉባዔ የፀደቀው የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ፣ የመረጃ ነፃነት...
Translate »