Etiópia

photo_2025-05-10_16-36-51.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-22 10:26:36
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia [ክቡር ሚኒስትሩ ከኢኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪዎቻቸው የቀረበላቸውን ሪፖርት አድምጠው ተጨማሪ ውይይት እያደረጉ ነው] ክቡር ሚኒስትር የቀረበው ሪፖርት እንደሚያስረዳው የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከታቀደው በላይ ውጤት አስገኝቷል። በትክልል። ክቡር ሚኒስትር ያስታውሱ እንደሆነ ሪፎርሙ ሲጀመር የዋጋ ንረትን ወደ ዘጠኝ በመቶ ዝቅ ማድረግ ይቻላል ብሎ የገመተ አልነበረም። ልክ ነው። እንኳን እኛ የሚደግፉን ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጭምር ተጠራጥረው ነበር። አሁን ግን ተችሏል። ከሁሉም የሚልቀው ስኬት ግን ይህ አይደለም። ምንድነው? ከእልህ አስጨራሽ ድርድር በኋላ ያለብንን የውጭ ዕዳ የመክፍያ ጊዜ ማራዘም መቻላችን ነው። ይህ ትልቅ ስኬት ነው። በዚህ ድርድር ያገኘነው የመክፈያ ጊዜ ማራዘሚያ ብቻ ነው እንዴ? አዎ። ክቡር ሚኒስትር። ዕዳችንን አልሰረዙልንም? አልተሰረዘም። የመክፈያ ጊዜያቸው የደረሱ ብድሮች እስከ 14 ዓመታት እንዲራዘም ነው የተወሰነልን። ታዲያ ይህንን ነው ትልቅ ስኬት ያልከው? አዎ። በጣም ትልቅ ስኬት ነው ክቡር ሚኒስትር። እንዴት እንደ ትልቅ ስኬት ይቆጠራል? ይቆጠራል ብቻ ሳይሆን ትልቅ ስኬት ነው። ለምን? የውጭ ዕዳችን መክፈያ ጊዜ ተራዘመ ማለት… እ…? ተጨማሪ አቅም ይፈጥርልናል።...
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-22 03:39:43
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ እ.ኤ.አ. እስከ 2040 ድረስ በዓለም ላይ ካሉ 20 ቀዳሚና ተወዳዳሪ የአቪዬሽን ተቋማት አንዱ ለመሆን፣ ዓመታዊ ገቢውንም ወደ 29 ቢሊዮን ዶላር ለማሳደግ ያለውን ግዙፍ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ይፋ አደረገ። አየር መንገድ ግሩፑ ዕቅዱን ይፋ ያደረገው ከሚያዚያ 9 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. የቆየው፣ የኢትዮጵያ የመሠረተ ልማትና ኮንስትራክሽን ሳምንት መክፈቻ ሥነ ሥርዓት፣ በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ሲካሄድ ነው። ‹‹እንደ አገር የመሠረተ ልማት ግንባታን እንዴት እንመራለን?›› በሚል መነሻ ሐሳብ፣ የኢትዮጵያ የአየር መንገድ ለ80 ዓመታት በዘርፉ ያለውን ልምድ አጋርቷል። የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ ባቀረቡት ማብራሪያ መሠረት፣ አየር መንገዱ አሁን ያለውን 7.6 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢ በማሳደግ እ.ኤ.አ. እስከ 2040፣ 29 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ግብ አድርጎ እየሠራ መሆኑ ገልጸዋል። በ“ራዕይ 2040” ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ዋና ዋና ዓላማዎች መካከል አሁን ያለውን የአውሮፕላኖች ብዛት ከ145 ወደ 356 ማሳደግ፣ የመዳረሻዎችን ብዛት አሁን ካለው የዓለም አቀፍ መዳረሻዎች ከ144 ወደ 290 እና የአገር ውስጥ መዳረሻዎች ከ24 ወደ 47 ለማድረስ ታቅዷል ተብሏል።...
Telecom.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-22 03:38:38
ፍላጎቱን ለማሳካት አምስት ቢሊዮን ዶለር ያስፈልጋል ብሏል በኢትዮጵያ የሚታየውን የዲጂታል ኢኮኖሚ ፍላጎት ለማሟላት በመጪዎቹ ሁለትና ሦስት ዓመታት፣ አሁን በሥራ ላይ ያለውን የቴሌኮም መሠረተ ልማት በእጥፍ ማሳደግ እንደሚገባ፣ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሳሰቡ፡፡ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄለፑት ይህን የተናገሩት፣ ከሚያዝያ 12 ቀን እስከ ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በተካሄደው የአውሮፓ ኅብረትና የኢትዮጵያ ቢዝነስ ፎረም ነው፡፡ ‹‹የቴሌኮም ኢንዱስትሪው በመሠረተ ልማት ግንባታ ትልቅ ሚና ይፈልጋል›› ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ ሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ ከገባ ገና አምስት ዓመታት ቢሆነውም ዘርፉ በርካታ ዕድሎች አሉት ብለዋል፡፡ ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ያሏትን 15 ሺሕ የቴሌኮም ማማዎች አሁን ካለው አገራዊ ፍላጎትና ምኞት ጋር ለማጣጣም ከተፈለገ፣ መሠረተ ልማቱ በመጪዎቹ ሁለትና ሦስት ዓመታት በእጥፍ መጨመር አለበት ሲሉ አስረድተዋል፡፡ መሠረተ ልማቱን ለማሟላት እስከ አምስት ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በግማሽ ቢሊዮን ዶላር ያህል የቴሌኮም መሠረተ ልማት ግንባታ ውስጥ ገብቷል ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ ነገር ግን አጠቃላይ የቴሌኮም ኢንዱስትሪው አምስት ቢሊዮን ዶላር ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ይፈልጋል ብለዋል፡፡ ስኬታማና...
Kin-Bahil.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-20 16:01:13
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia ሚስ አፍሪካን የቁንጅና ውድድር አዲስ አበባ ሁለተኛውን የ”Miss African Essence International 2026″ የቆንጅና ውድድር ልታስተናግድ መሆኑን ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ​የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ ከማሂ ኢቨንትስ ጋር በመተባበር የሚዘጋጀው የቁንጅና ውድድር አፍሪካውያን ሴቶች የሚታደሙበት ሲሆን፣ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በወዳጅነት ፓርክ የሚጀመር ይሆናል፡፡ The post ሚስ አፍሪካን የቁንጅና ውድድር first appear on ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 reliable news source in Ethiopia and is written by በጋዜጣው ሪፓርተር Source link
Mekides.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-20 16:00:22
የ50 ሺሕ ብር ቅጣትና ለሁለት ወራት ከሥምሪት ይታገዳሉ ተብሏል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን፣ ሶዶ ከተማ ነዳጅ ቀድተውና ሥምሪት ወስደው ለሕዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት በማይሰጡ ተሽከርካሪዎች ላይ ዕርምጃ እየወሰደ መሆኑን፣ የሶዶ ከተማ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምርያ አስታወቀ፡፡  የሶዶ ከተማ ትራንስፖርትና ሎጂቲክስ መምርያ ኃላፊ ወ/ሪት መቅደስ በዛብህ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ለሕዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡና ሥምሪት የወሰዱ አንዳንድ ተሽከርካሪዎች ነዳጅ ከቀዱ በኋላ ወደ መናኸሪያ ገብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ አይደሉም፡፡ ጥቂት የማይባሉ አሽከርካሪዎችም መናኸሪያ ውስጥ ተሽከርካሪዎቻቸውን በማቆም ከእነ ረዳቶቻቸው እየተደበቁ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በመሆኑም የከተማው ትራንስፖርት መምርያ መናኸሪያ ግቢ ውስጥ ተሽከርካሪዎቻቸውን አቁመው የተሰወሩትን በመለየት ሰሌዳቸውን ፈቶ ዕርምጃ እየወሰደ የሚገኝና በቀጣይም በእንዲህ ዓይነት ተግባር በተሰማሩ ተሽከርካሪዎች ላይ የ50 ሺሕ ብር ቅጣት፣ እንዲሁም ለሁለት ወራት ከሥምሪት መርሐ ግብር የሚያግዳቸው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ‹‹የከተማው ትራንስፖርት መምርያ ያለውን የነዳጅ እጥረት ችግር ለመቅረፍ ተሽከርካሪዎች ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀሙ የማድረግ ሥራዎች እየሠራ ይገኛል፤›› ያሉት ኃላፊዋ፣ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች በማደያዎች ቅድሚያ አግኝተው እንዲስተናገዱ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ የሚሠራው ሥራ አንዱ ተጠቃሽ ነው ብለዋል፡፡ ወ/ሪት መቅደስ እንደተናገሩት፣...
Gurage.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-19 23:51:29
የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ክትፎን ጨምሮ ከጉራጌ ማንነት መገለጫ ውስጥ የሚጠቀሱትን አራት ዕሴቶች በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም አቀፍ ቅርስነት ለማስመዝገብ ከ2016 ዓ.ም. ጀምሮ እየሠራ ይገኛል፡፡ ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. የጉራጌ ዞን መስተዳድር ምክር ቤት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራትን በወልቂጤ ከተማ በገመገመበት ወቅት ሪፖርት ያቀረቡት የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ መሠረት አመርጋ እንደገለጹት፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከተከናወኑ ሥራዎች የጉራጌ ማኅበረሰብ መገለጫ ከሆኑት የተወሰኑትን በማስቀደም በዩኔስኮ የማስመዝገብ ሥራዎች መከናወናቸው ይገኙበታል፡፡ ይህንን አስመልክቶ ከሪፖርተር ጋር ቃለ መጠይቅ ያደረጉት ወ/ሮ መሠረት፣ የጉራጌ ማኅበረሰብ ከጥንት ጀምሮ በርካታ መገለጫዎች ያሉትና ባህልና ታሪክን ገንብቶ ለትውልድ ያሻገረ ቢሆንም፣ ከጢያ መካነ ቅርስ በስተቀር አብዛኞቹ ቅርሶቹ በአገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመዝግበው እንደማይገኙ ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ማኅበረሰቡ ካሉት ቅርሶች የተወሰኑት ቢወጡና በዩኔስኮ የቅርስ መዝገብ ቢመዘገቡ ዓለም ይማርባቸዋል፣ እንደ አገርም ለቱሪዝም ዘርፍ ይጠቅማል፣ እንደ ማኅበረሰብም ዕሴቱ እንዲታወቅ ይረዳል በሚል ከ2016 ዓ.ም. ጀምሮ ከቅርስ ባለሥልጣንና ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመሆን ሥራ መጀመሩን...
Social-1-1.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-19 23:50:18
የአገር ውስጥ የንግድ ምልክት ያገኙ ምርቶችና አገልግሎቶች 14,914 ናቸው ተብሏል በኢትዮጵያ የፈጠራ ሥራ ባለቤትነት ብቸኛ መብት (ፓተንት) ጥበቃ የሚደረግላቸው የፈጠራ ሥራዎች ብዛት ከአንድ ሺሕ እንደማይበልጥ፣ የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡ ባለሥልጣኑ ይህን የገለጸው የአዕምሯዊ ንብረት ዘርፍን፣ ተቋሙንና አገልግሎቶቹን በተመለከተ ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ከመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ጋር በቢሾፍቱ ከተማ ውይይት ሲያደርግ ነው። በውይይቱ ወቅት በንግድ ምልክት፣ በቅጅና ተዛማጅ፣ እንዲሁም በፈጠራ ሥራዎች የአዕምሯዊ መብት ምዝገባ ላይ ከፍተኛ የግንዛቤ ማነስ ችግር እንዳለ ተገልጿል። የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ እንዳሉ ሞሲሳ፣ ባለሥልጣኑ በኢንዱስትሪያዊ ንብረትና በቅጅና ተዛማጅ መብቶች ዘርፍ ሥር ሦስት አዋጆችን ማለትም የፈጠራ ሥራ ብቸኛ መብት (ፓተንት)፣ የንግድ ምልክትና ኢንዱስትሪያዊ ንድፍ የሚሉትን እያስተዳደረ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪ የጂኦግራፊያዊ ምንጭ አመልካቾች አዋጅ በቅርቡ ፀድቆ ወደ ሥራ ይገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል። ባለሥልጣኑ በኢትዮጵያ የፈጠራ ሥራ ባለቤትነት ብቸኛ መብት (ፓተንት) ጥበቃ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አገር መሆኗ እንደሚነገር፣ ሆኖም ጥበቃ የሚደረግላቸው የዜጎች ፈጠራ ሥራዎች ብዛት በጣም ዝቅተኛ መሆኑንና...
Civic-1.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-19 17:10:33
የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን በዓለም አቀፍ መመዘኛዎች መሠረት፣ ሽብርተኝነትን በገንዘብ በመደገፍ ለሥጋት ተጋላጭ ናቸው ተብለው የተለዩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ክትትል እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ድጋፍ የሚያገኙት ከፍተኛ ሥጋት ተብለው ከተለዩ አካባቢዎች ከሆነ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሠሩበት አካባቢ ግጭት ያለበት ከሆነና ድንበር አካባቢ የሚገኝ ወይም በተለያዩ መመዘኛዎች ከሽብርተኝነት ጋር የተያያዘ ጉዳይ ይኖራል ተብሎ የሚገመት ከሆነ፣ ክትትል እንደሚደረግ፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ድርጅቶቹ በዓለም አቀፍ መመዘኛ መሠረት የሚያገኙት የገንዘብ ድጋፍ ከፍተኛ በሆነ መጠን ሥጋቱም ይጨምራል ተብሎ ስለሚገመት፣ ክትትሉ እንደሚከናወንና ነገር ግን፣ ‹‹ሁሉም የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመደገፋቸው ሥጋት ውስን በመሆኑ ተጋላጭነታቸውም በጣም አነስተኛ ነው፤›› ብለዋል፡፡ የክትትል ሥራ የሚከናወነው በሁሉም የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ እንዳልሆነ፣ ሽብርተኝነትን በገንዘብ የሚደግፉ ድርጅቶች ተገኝተው ሳይሆን ተጋላጭ ሊሆኑ ይችላሉ የሚባሉት በመለየታቸው እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ባለሥልጣኑ የጥንቃቄ ዕርምጃ እየወሰደ ነው፤›› ያሉት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፣ በመሥፈርቱ መሠረት ተጋላጭ ይሆናሉ ተብለው ለተለዩ ድርጅቶች ግንዛቤ ከማስጨበጥ ጀምሮ የክትትልና የቁጥጥር ሥራ እንደሚከናወን አስረድተዋል፡፡ ‹‹አንዳንድ...
1776629377_IMF.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-04-19 17:09:35
የዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ያስመዘገበችው የኢኮኖሚ ዕድገት ጠንካራ ቢሆንም፣ የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት የኑሮ ውድነት እንደሚያስከትልና የምግብ ዋስትና ሥጋትን ውስጥ እንደሚጥል አስታወቀ፡፡ አይኤምኤፍ ሥጋቱን የገለጸው ከሰሀራ በታች የአፍሪካ አገሮች የኢኮኖሚ ትንተና ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ይፋ ሲያደርግ ነው፡፡ እ.ኤ.አ. በ2025 የቀጣናው አገሮች ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገባቸውን የሚገልጸው የአይኤምኤፍ ትንተና፣ 4.5 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት መመዝገቡንና ኢትዮጵያም ባደረገችው የማክሮ ኢኮኖሚ ለውጥ ምክንያት ከፍተኛ ዕድገት ካስመዘገቡ አገሮች መካከል ከቀዳሚዎች ተርታ ትሠለፋለች ብሏል፡፡ ሆኖም የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት ቀውስ ከፍተኛ ሥጋት መፍጠሩን፣ በተለይም በነዳጅና በምግብ ዋጋ ላይ ከባድ አደጋ መደቀኑን አስረድቷል፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ነዳጅ ከውጭ የሚያስገቡ አገሮች ኢኮኖሚ እንደሚፈተን የሚገልጸው አይኤምኤፍ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ፣ የማዳበሪያ፣ የመርከብ ኪራይ ዋጋ ንረት ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ሸቀጦች ዋጋ እንዲጨምር ምክንያት እንደሚሆን፣ በተለይም በትራንስፖርትና በግብርና ምርቶች ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ እንደሚፈጥር አስጠንቅቋል፡፡ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አስተዋጽኦ ተጨምሮበት እ.ኤ.አ. በ2025 ከፍተኛ ዕድገት አስመዝግቦ የነበረው የቀጣናው ጠንካራ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ እ.ኤ.አ. በ2026 ወደ 4.3 በመቶ እንደሚቀንስ ተገልጿል፡፡ ይህ ሁኔታ...
Election.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-04-19 09:53:18
ሲቪል ሰርቪሱ ከፖለቲካ ጫና እንዲላቀቅ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጠይቀዋል የብቃት ክፍተት፣ የመንግሥት መክፈል አቅምና ደካማ ሥራ ባህል ዋነኛ የሲቪል ሰርቪስ ፈተናዎች መሆናቸውን፣ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር ገለጹ፡፡ ኮሚሽነሩ መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ይህን የተናገሩት መልካም አስተዳደር ለአፍሪካ (Good Governance Africa) የተሰኘ የምሥራቅ አፍሪካ ቅርንጫፍ፣ መጪውን አገራዊ ምርጫ አስመልክቶ ስለሲቪል ሰርቪሱ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ነው፡፡  ተቋሙ ሰባተኛው አገራዊ ምርጫን አስመልክቶ አካሂዳቸዋለሁ ካላቸው ውይይቶች የመጀመሪያ የሆነውን፣ ‹‹በኢትዮጵያ መልካም አስተዳደርን ለማጎልበት የሲቪል ሰርቪሱ ሚና›› በሚል ርዕስ ከፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ በውይይቱ ወቅት የብልፅግና ፓርቲ፣ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ዋነኛ ፓናሊስት ነበሩ፡፡ የብቃት ክፍተት የሁሉንም አካላት ርብርብ፣ ቅንጅት፣ መተባበርና የመንግሥት ሠራተኛውን መሰጠት የሚጠይቅ ጉዳይ መሆኑን ኮሚሽነር መኩሪያ (ዶ/ር) አስረድተዋል፡፡ የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ባህል መቀየር አለበት ያሉት ኮሚሽነሩ፣ ዓላማ ያለው፣ አገር የመገንባት ትልምን የያዘና ሁሉንም የማገልገል ባህል መፈጠርን የሚጠይቅ ነገር ግን ፈታኝ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የመንግሥት ሠራተኞችን ደመወዝ ማሻሻል የመንግሥት የመክፈል አቅም ከአጠቃላይ የአገር ዕድገት...
Translate »