Etiópia

Market-2.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-28 00:18:19
በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የኢትዮጵያ ሸማች ከምንጊዜውም በላይ ከባድና ተደራራቢ የኢኮኖሚ ፈተናዎች ውስጥ ይገኛል። አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የብር የመግዛት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ መዳከሙ፣ የነዳጅ ዋጋ መናሩና የቤት ኪራይ ዋጋ ጣሪያ መንካቱ ሳያንስ፣ በቅርቡ ይፋ የተደረጉት የመንግሥት መሠረታዊ አገልግሎቶች የታሪፍ ጭማሪዎች በሸማቹ ጫንቃ ላይ ወድቀዋል፡፡ መንግሥት ለዜጎች የሚያቀርባቸው አገልግሎቶች ማኅበራዊ ፍትሕን ለማረጋገጥ የሚቀርቡ መሠረታዊ መብቶች ቢሆኑም፣ አሁን በመንግሥት በኩል በጅምላ የታዩት የዋጋ ጭማሪዎች የሕዝቡን የደመወዝ ወለልና የመክፈል አቅም ያላገናዘቡ ናቸው የሚሉ አስተያየቶች ይቀርባሉ። የኢትዮጵያ የሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት መሥራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ቁምላቸው አበበ፣ በአገሪቱ ስላለው የኑሮ ውድነት ለሪፖርተር ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተከሰተው የኑሮ ውድነትና የዋጋ ግሽበት በይበልጥ እያሻቀበ የመጣው የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑን ገልጸዋል። ከማሻሻያው በፊት የኑሮ ውድነት የነበረ ቢሆንም፣ የፖሊሲ ለውጡ ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ በነዳጅ፣ በዘይት፣ በዱቄት፣ በስኳርና በሌሎች መሠረታዊ ሸቀጦች ላይ ይደረግ የነበረው የመንግሥት ድጎማ ሙሉ በሙሉ መነሳቱ ችግሩን በከፍተኛ ሁኔታ እንዳባባሰው አስረድተዋል። ከዚህም በተጨማሪ የዶላር ምንዛሪ መለቀቅ የብርን የመግዛት አቅም...
Business-2.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-24 17:21:47
ጥቃቅንና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ራሱን የቻለ ስታንዳርድ እንደሚወጣላቸው ተገልጿል እ.ኤ.አ. ከ2030 ዓለም አቀፍ የሒሳብ ሪፖርት አቀራረብ ዘላቂነትን የተመለከቱ ሁለት ስታንዳርዶች (International Financial Reporting Standard-Sustainability Disclosure Standards) ትግበራ አስገዳጅ እንደሚሆን፣ የኢትዮጵያ ሒሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ አስታወቀ፡፡ ቦርዱ ይኼን ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አቀራረብ ስታንዳርዶች (Sustainability Disclosure Standards – IFRS) የዘላቂነት ትግበራ ፍኖተ ካርታ ይፋ ማድረጊያ ሁለተኛ ዙር ዓውደ ጥናት፣ ከሰኔ 15 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ሲካሄድ ነው። የኢትዮጵያ ሒሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ፅዋዬ ሙሉነህ፣ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የሒሳብ ሪፖርት አቀራረብ ስታንዳርድን በአዋጅ በተደነገገው መሠረት እየተገበረች እንደምትገኝ፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ ከፋይናንስ ባሻገር ዘላቂነት ላይ ያተኮሩ (IFRS S1) እና (IFRS S2) የተሰኙ ስታንዳርዶችን እንዲተገበሩ ልታደርግ እንደሆነ ገልጸዋል። ዓለም አቀፉ የሒሳብ ሪፖርት ደረጃ ዘላቂነት ስትራቴጂካዊ ፍኖተ ካርታ ሲወጣ አገሮች መቼ መተግበር አለባቸው የሚለውን ዕድል መስጠቱን የተናገሩት ወ/ሮ ፅዋዬ፣ በኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. ከ2024 ጀምሮ ሁለት ዓመት ወስዶ ሲዘጋጅ እንደነበር፣ እ.ኤ.አ. በ2030 ሙሉ ለሙሉ መተግበር ይሮርባታል ተብሎ መፅደቁን አስረድተዋል። ሆኖም አቅም...
IMG_20260624_200519_603.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-24 17:20:41
የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም፣ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚደረግባቸውን አጀንዳዎች ለሕዝብ ይፋ አደረገ። የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕሮፌሰር)፣ ኮሚሽኑ ባለፉት አራት ዓመታት ከ200 ሺሕ በላይ ዜጎችን በማወያየት ለአገራዊ ጉባኤው ስምንት አገራዊ አጀንዳዎች መለየታቸውን ገልጸዋል። በዚህም፣ የአገር ግንባታ የማንነትና የአገር ጉዳዮች፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ የፌዴራል ከተሞች አዲስ አበባና ድሬዳዋ፣ የሃይማኖት ጉዳዮች፣ የተቋማት ግንባታና ሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ፣.ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የአርሶአደርና አርብቶ አደር ጉዳዮች፣ ሙስናና መልካም አስተዳደር የፀረ ሙስና ሥርዓት ግንባታ እና   ሰላም ግንባታና የግጭት መንስኤዎች አፈታት መንገዶች በአገራዊ ምክክር  ጉባኤው ምክክር የሚደረግባቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች ሲሆኑ፣ በውስጣቸው ዝርዝር ንዑስ አጀንዳዎች እንደተካተቱባቸው ተነግሯል። አጀንዳዎቹ አገራዊ ተብለው የተመረጡ ዋና ዋና ጉዳዮች መሆናቸውን የገለጹት ዋና ኮሚሽነሩ፣ ምክክሩ የሁሉንም ጥረት ስለሚፈልግ ሒደቱ እንዲሳለጥ ንቁ ተሳትፎ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል። ንዑስ አጀንዳዎቹም፣ የሽግግር ፍትሕ፣ የጊዜያዊ ተኩስ አቁም ጉዳይ፣ የማንነትና የአገር ጉዳዮች፣ የታሪክ ጉዳዮች፣ የቋንቋ ጉዳዮች፣ የምርጫ ሥርዓት፣ የባለሥልጣናት የሥልጣን ዘመን፣ የአዳዲስ ክልሎች...
Politics-1-1.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-24 11:04:41
በስደተኝነትና በጥገኝነት ጠያቂነት ኢትዮጵያ ውስጥ የተጠለሉ ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን ፍላጎት ለማሟላት፣ ከሰብዓዊ ዕርዳታ በተጨማሪ የልማት ፋይናንስ እንደሚያስፈልግ የመንግሥት ባለሥልጣናት ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ ጥሪ አቀረቡ፡፡ ጥሪው የቀረበው የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ከፌዴራልና ከክልል መንግሥታት፣ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የስደተኞች ኤጀንሲ፣ እንዲሁም ከአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ያዘጋጀውን ‹‹ማካተት›› የተሰኘ ፍኖተ ካርታ ይፋ ሲደረግ ነው፡፡ ፍኖተ ካርታው ስደተኞችንና ስደተኛ ተቀባይ ማኅበረሰቦችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርግና ከሰብዓዊ ዕርዳታ ባለፈ፣ ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት የልማት ፋይናንስ አማራጮችን ለማፈላለግ የሚረዳ ነው ተብሏል፡፡ በመድረኩ የተገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ታገሰ ጫፎ ባደረጉት ንግግር፣ ኢትዮጵያ በጦርነትና በሚደርስባቸው ሥቃይ ምክንያት ከአገራቸው ተሰደው የሚመጡ ስደተኞችን በንቃት ተቀብላ እያስተናገደች ነው ብለዋል፡፡ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በኢትዮጵያ ከሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ባሻገር፣ ተገማችና ለበርካታ ዓመታት የሚያገለግል የልማት ፋይናንስ ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አድርገዋል፡፡ ‹‹አገራዊ ልምድን በመያዝ ከባድ የሚባል ሰብዓዊ ቀውስን ወደ ጋራ ቀጣናዊ ልማት መለወጥ እንችላለን፤›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ‹‹ማካተት›› የተሰኘው ፍኖተ ካርታ፣ ‹‹መደመር በተሰኘው ፍልስፍና ውስጥ ያለ ዕሳቤ ነው›› ያሉት...
Tesfaye.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-24 11:03:30
በ12 የምርጫ ክልሎች ደግሞ ድጋሚ የድምፅ ቆጠራ ይካሄዳል ተብሏል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጉልህ የሆነ የምርጫ ሕግ ጥሰት እንደተፈጸመባቸው አረጋግጫለሁ ባለባቸው 11 የምርጫ ክልሎች ድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ መወሰኑን አስታወቀ፡፡ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ማሳወቂያ መርሐ ግብር ላይ ነው ይህንን ያስታወቀው፡፡ የምርጫውን ሒደትና ጠቅላላ ውጤት ይፋ ያደረጉት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ንዋይ፣ ምርጫ ከተደረገባቸው 1‚139 የሕዝብ ተወካዮችና የክልል የምርጫ ክልሎች መካከል በ11 የምርጫ ክልሎች ጉልህ የምርጫ ሕግ ጥሰት መፈጸሙን ቦርዱ በማረጋገጡ ድጋሚ ምርጫ እንዲደረግ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡ ድጋሚ ምርጫ ይደረግባቸዋል ከተባሉት የምርጫ ክልሎች መካከል፣ በሶማሌ ክልል የሚገኙ ለክልል ምክር ቤት ምርጫ ተደርጎባቸው የነበሩ አምስት የምርጫ ክልሎች ይገኙበታል፡፡ እነሱም ሀርገሌ፣ ዳሮ፣ ሀዲጋላ፣ አዋሬና ዳራቶሌ ምርጫ ክልሎች ናቸው፡፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵየያ ክልል ሶሮ አንድና ጠንባሮ ምርጫ ክልል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ በኦሮሚያ ክልል ባቱ ዝዋይና ቤጊ ምርጫ ክልሎች ለሕዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት ድጋሚ ምርጫ እንዲደረግባቸው የተወሰነባቸው የምርጫ ክልሎች መሆናቸውን አቶ ተስፋዬ አስረድተዋል፡፡ በሲዳማ ክልል አሮሬሳ ምርጫ...
Social-66-1.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-24 04:39:58
ሐሰተኛ የሒሳብና የኦዲት ሪፖርት ማቅረብን ጨምሮ 13 ያህል የሕግ ጥሰቶችን የፈጸሙ 47 የሒሳብና ኦዲት ባለሙያዎች፣ ሪፖርት አቅራቢ ድርጅቶችና አካላት የተለያየ ሕጋዊ ዕርምጃ እንደተወሰደባቸው፣ የኢትዮጵያ ሒሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ገለጸ፡፡ የቦርዱ የሕግ ማስከበር ዳይሬክቶሬት ተጠባባቂ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዘውዱ ጌታቸው ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ቦርዱ ከሐምሌ 2017 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ሰኔ ወር 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በሒሳብና በኦዲት ባለሙያዎች፣ ሪፖርት አቅራቢ አካላትና ድርጅቶች ላይ ክትትል አድርጓል። የሒሳብና የኦዲት ሪፖርትን ደረጃውን ጠብቆ ባለመሥራት ሁለት፣ ከቦርዱ የተሰጠ የሙያ ፈቃድ ሳይኖራቸው ሐሰተኛ የሒሳብና የኦዲት ሥራ ፈቃድ ማዘጋጀትና መጠቀም ሦስት፣ የወሰዱትን ፈቃድ ለቦርዱ ተመላሽ ሳያደርጉ ተቀጥሮ መሥራት አምስት፣ ለኦዲት ሥራ ጥራት ምርመራ፣ ቁጥጥርና ክትትል ሥራ ተባባሪ ባለመሆን ሁለት፣ የደንበኞችን ሥራዎች ወይም ሪፖርቶች ከቦርዱ ፈቃድ በሌለው ሰው ተፈርመው እንዲወጡ ማድረግ አንድ በአጠቃላይ 13 የሕግ ጥሰቶች መፈጸማቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ሕጋዊ ዕርምጃ እንደተወሰደባቸው አስረድተዋል። በራስ ባልተዘጋጀ የሒሳብ መግለጫ ፊርማና ማኅተም በማድረግ ሁለት፣ የሙያ ፈቃድን ለሌላ ሰው አሳልፎ መስጠት ወይም የሙያ ሥራን በውክልና በማሠራት ሁለት፣ ሐሰተኛ መረጃ በማቅረብ ወይም...
Business-1.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-24 04:38:51
በኢትዮጵያ የቤት ሠራተኛና አሠሪዎችን የተመለከቱ ጉዳዮችን በግልጽ የሚመራ የሕግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ፣ ዕድሜያቸው ለሥራ ያልደረሱ ሕፃናት ለቤት ውስጥ ሠራተኝነትና ቤት ውስጥ ለሚፈጸም የመብት ጥሰት እየተዳረጉ መሆናቸው ተገለጸ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ5.6 ሚሊዮን በላይ የቤት ሠራተኞች አሉ ተብሎ እንደሚገመት፣ የቤት ሠራተኞችን የቅጥር ሁኔታ፣ ጥቅማ ጥቅም፣ የሥራ ስምምነትና የሥራ ከባቢን ጨምሮ በሚገባ የሚያስተዳድርና የሚመራ ራሱን የቻለ ሕግ አለመኖሩ ተጠቅሷል፡፡ ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ የተሰኘው አገር በቀል ድርጅት ለረዥም ጊዜ ሲጠበቅ እንደ ነበር የተገለጸው የቤት ውስጥ ሠራተኞችን የተመለከተ ሕግ እንዲወጣ ሲካሄድ በቆየው ውትወታ፣ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እየተዘጋጀ ነው የተባለ አዲስ ረቂቅ ሕግ ላይ የፖሊሲ ውይይት መድረክ ትናንት ማክሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. አዘጋጅቶ ነበር፡፡ በውይይቱ የተሳተፉ አንድነት የሴት ሠራተኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ሒሩት አበራ ስለጉዳዩ ሲያብራሩ፣ በኢትዮጵያ አሥር ክልሎች ማኅበራቸው እየተንቀሳቀሰ ቢሆንም በየቤቱ ያለው የሠራተኞች አያያዝ ለመደራጀት ቀርቶ መብት ለመጠየቅ አስቸጋሪ ነው ብለዋል፡፡ ሁሉንም ሠራተኞች አባል ለማድረግ አዳጋች መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንቷ በመላ አገሪቱ አሉ ከሚባሉ የቤት ሠራተኞች ውስጥ 94,000 ያህሉ አባላት መሆናቸውንና በአገሪቱ ሕግ...
Translate »