Etiópia

Culture-44.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-06 18:40:59
ዞሲማስ ሚካኤል በፌዴራላዊ ሪፐብሊኩ 7ኛ አገራዊ ምርጫ ላይ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ምርጫ ድምፃቸውን  በመኖሪያ ሠፈራቸው ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሰጡ መራጮች አንዱ ናቸው። በስድሳዎቹ አጋማሽ ዕድሜያቸው ላይ የሚገኙት አቶ ዞሲማስ፣ በኢትዮጵያ መንግሥታት የፓርላማ ምርጫ የሰባ ዓመታት ጉዞ ውስጥ ከተካሄዱት 13 አገራዊ ምርጫ መካከል በንጉሠ ነገሥት መንግሥት ዘመን የተካሄደውን አምስተኛውንና የመጨረሻውን ምርጫ ላይ ድምፅ ባይሰጡም፣ በወቅቱ የነበረውን በከተማዪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተደረገውን የግለሰቦች የምረጡኝ ቅስቀሳ ያስታውሳሉ። በቅድስት በአታ ለማርያም ገዳምና በፓርላማው መካከል ይገኝ የነበረው ‹‹የሕገ መንግሥት አደባባይ›› ከአዋሬ ወደ ቤልኤር በሚወስደው መንገድ በስተግራ ከሚገኘው ‹‹ምሥራቅ ማዘጋጃ ቤት›› (በዘመነ ደርግ የምሥራቅ ዞን ትምህርት ቤቶች ጽሕፈት ቤት ሆኖ ነበር) እስከ ካዛንቺስ የዕጩዎች የምረጡኝ ፖስተሮች በየአጥሩ ላይ መለጠፋቸውን ያስታውሳሉ። ይማሩበት የነበረው አስፋ ወሰን አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤትንና የግንፍሌ ወንዝን  የሚጎራበቱት  የ1965 ዓ.ም. ዕጩ ተወዳዳሪው  አቶ ግርማቸው ፊሊክስ የብራዚል ስሪት የሆነችው ቮልስ ቫገን አውቶሞቢላቸውን እያሽከረከሩ ካዛንቺስ ቶታል አጠገብ ላይ ሆነው ‹‹ምረጡኝ›› እያሉ ሲቀሰቅሱም  ያስታውሳሉ። የሥርዓተ ዘውድ ሕገ መንግሥትና ምርጫው...
Adanech-44.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-04 20:42:32
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደው በ7ተኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ በአዲስ አበባ ከሚገኙ 23 ምርጫ ክልሎች በተወሰኑት ሪፖርተር በመዘዋወር ቅኝት አድርጓል፡፡ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ምርጫ ክልል 24 ወረዳ አምስት በሚገኘው ሠፈረ ሕይወት ዕድር ቤት ምርጫ ጣቢያ አምስት፣ ዘንባባ ዕድር ቤት ምርጫ ጣቢያ ስድስት፣ ራዕይ ሸማቾች ምርጫ ጣቢያ ሁለት፣ መጢ ዕድር ቤት ምርጫ ጣቢያ ሦስት በተደረገ ቅኝት በአብዛኛው ተመሳሳይ የሆኑ ክስተቶችን ለመታዘብ ተችሏል፡፡ በሠፈረ ሕይወት ዕድር ቤት ምርጫ ጣቢያ አምስት ከጠዋቱ 12 ሰዓት ቀድመው በብዛት የተገኙት በዕድሜ የገፉ እናቶችና አባቶች ነበሩ፡፡ በግቢውና ከግቢው ውጪ ባሉ ሁለት ድንኳኖች ውስጥ ሞልተው ከሚታዩት በተጨማሪ፣ ከውጭ አግዳሚ ወንበር ላይ ተቀምጠው ወረፋ የሚጠባበቁም ነበሩ፡፡ በማለዳው በርካታ መራጮች ወረፋ ሲጠብቁበት በነበረው በዚሁ ጣቢያ፣ የድምፅ መስጠት ሥነ ሥርዓቱ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ላይ ነበር የጀመረው፡፡ በሰው ተደግፈው ለሚመጡ፣ ከዘራ ለያዙ እናቶችና አባቶች ቅድሚያ በመስጠት ሲካሄድ በነበረው የምርጫ ሒደት ካርዳቸው የጠፋባቸው፣ በኦንላይን ተመዝግበው መረጃ ያልተገኘላቸው መፍትሔ ለማግኘት ሲጠይቁና ካርድ የጠፋባቸው ሲመለሱ ታይተዋል፡፡  በዚህ ጣቢያ ማልደው የተገኙት አዛውንቶች ቢሆኑም፣...
Adama.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-04 20:41:13
በኤልያስ ክፍሌ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባን የጊዜ ገደቦች ሲያራዝም፣ ብዙዎች የድምፅ መስጫው ቀንም እንደሚራዘም ሲገምቱና ቀኑ እንዲገፋ የጠየቁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ቢኖሩም፣ ምርጫው ግን ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ተከናውኗል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ዋና ከተማ አዳማ የሚገኙ በርካታ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤትም ይፋ አድርገዋል። የድምፅ አሰጣጥ ሒደቱ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምሽት 12 ሰዓት መርጠው በጨረሱ ጣቢያዎች ውጤት ከንጋቱ 12 ሰዓት መለጠፍ ቢገባውም፣ እስከ ማለዳው አንድ ሰዓት ድረስ ሳይለጠፍ የተመለከትናቸው ጣቢያዎችም ነበሩ። የከተማው መደበኛ እንቅስቃሴ በምርጫው ዋዜማ እሑድ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ከግማሽ ቀን በኋላ ወደ አመሻሹ የሞተር ብስክሌትና የባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ፣ በትራፊክ ፖሊሶችና በትራንስፖርት ጽሕፈት ቤት ሥምሪቶች ሲገደብ ተመልክተናል። ምንም እንኳን በምርጫ ጣቢያዎች አቅራቢያ በጣት የሚቆጠሩ የኦሮሚያ ፖሊስ፣ እንዲሁም የሚሊሻ አባላት የተገኙ ቢሆንም፣ እሑድ ከሰዓት በኋላ በዋና ጎዳና የፌዴራል ፖሊስ ፓትሮሎችን ጨምሮ የክልሉ ፖሊስ፣ ሚሊሻና የማኅበረሰብ ፖሊስ አገልግሎት የሚሰጡ ‹‹አስተባባሪ›› የሚል መለያ ያደረጉ በስፋት ተስተውለዋል። አዳማ ከተማ ከምርጫው አስቀድሞ...
Aketse.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-04 14:05:24
7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ደፋ ቀና ስትል የከረመችው አዲስ አበባ ከተማ፣ በምርጫው ዋዜማ የተለየ እንቅስቃሴ አይስተዋልባትም ነበር፡፡ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ ምሽት 2 ሰዓት ገደማ ባደረግነው ቅኝት፣ የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ቅድመ ዝግጅት፣ መደበኛ የሰዎችና የንግድ ተቋማት እንቅስቃሴዎች እንደነበሩ የተመለከትን ሲሆን፣ የፀጥታ አካላትም ከወትሮው ባልተለየ መዲናዋን ሲጠብቁ ውለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ከተዘጋጁት 23 የምርጫ ክልሎች መካከል በምርጫ ክልል 2/14 እንዲሁም 12/13 በወረዳ 1 ኮንዶሚኒየም ግቢ፣ በወረዳ 3 ቤላ ወጣት ማዕከል የምርጫ ጣቢያዎች ባደረግነው ቅኝት፣ በምርጫ ጣቢያዎቹ መግቢያም ሆነ በዙሪያቸው የዕጩዎች ዝርዝር፣ ፎቶግራፍ፣ የምርጫ ምልክትም ሆነ የምርጫ ክልልና ጣቢያ መለያ ቁጥር አልተለጠፈም። አንዳንዶቹ በር ላይ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ጎልቶ በሚታይበት ቦታ ላይ ከመሰቀሉና ጥቂት ፖሊሶች ከመቆማቸው ውጪ የድምፅ መስጫ ድንኳኖች በመኖራቸው ብቻ የሚለዩ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ መነሻቸው ከፒያሳ፣ መገናኛ፣ ሜክሲኮና አዲሱ ገበያ ውጪ የሆኑ የምርጫ አስፈጻሚዎች ማደሪያ እንደተዘጋጀላቸው እንዲሁም ምርጫው በሚካሄድበት ዕለት የማይገኙ አስፈጻሚዎች ከእሑድ ግንቦት 23 ምሽት 12 ሰዓት በፊት እንዲያሳውቁ መልዕክት እንደተላከም ከአስፈጻሚዎች ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ብልፅግና ፓርቲን ወክለው...
Agegnew.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-04 14:04:03
ሰባተኛውን አገራዊ ምርጫ ለመዘገብ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ወደ ጎንደር ጉዞ የጀመረችው የሪፖርተር ሚዲያ ዘጋቢ፣ በአዲስ አበባ ይታይ የነበረው የመቀዛቀዝ ስሜት በጎንደር ከተማም ተቀብሏታል። ከከተማዋ በቅርብ ርቀት ላይ ከሚገኘው አውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ ባሉት መንገዶችና አደባባዮች ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው ዕጩዎችና የፓርቲውን የመወዳደሪያ ምልክቶች ከያዙ ባነሮች ውጪ፣ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን የሚያሳዩ አንድም ባነር አልነበረም። የፀጥታ ኃይሎች በከፍተኛ ቁጥር ይታዩ የነበረ ሲሆን፣ በተለይም በዋና ዋና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና የምርጫ ጣቢያዎች አቅራቢያ በብዛት ነበሩ። ሁለት የምርጫ ክልልና 240 የምርጫ ጣቢያዎች ያሏት የጎንደር ከተማ፣  በምርጫው ዋዜማ ዕለት የምርጫ ቁሳቁስ ከዋናው የማከማቻ ቦታ ወደ ሁለቱም የምርጫ ክልሎችና በኋላም ወደ ምርጫ ጣቢያዎቹ እስከ ምሽቱ 11 ሰዓት ተሠራጭቶ መጠናቀቁ ተገልጿል። የጎንደር ከተማ ከንቲባ የወትሮው የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እስከ 10 ሰዓት ድረስ የተለመደ ዓይነት የነበረ ቢሆንም፣ ከ10፡00 ሰዓት ጀምሮ ግን የባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ማቆማቸውንና የንግድ ሱቆችም በአብዛኛው ዝግ እንደነበሩ ተመልክተናል። በዋዜማው ከምሽት ጀምሮ የፀጥታ ችግር ሊከሰት ይችላል የሚል ሥጋት እንደነበር ሪፖርተር...
Hawassa.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-06-04 00:35:17
በያሬድ ንጉሤ በሲዳማ ክልል ምርጫ ጥቂት ቦታዎች ምርጫው እስከ እኩለ ሌሊት ስድስት ሰዓት ድረስ ሲሰጥ የነበረባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ነበሩ፡፡ የምርጫ ጣቢያዎች በጊዜ ካለመከፈት ጋር ተያይዞ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ሕዝቡ በሰዓቱ ድምፅ መስጠት እንዳልቻለም፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ተወካዮች ገልጸዋል፡፡ የሲዳማ ክልል ሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ገነት ማርቆስ፣ ‹‹እኔ በግሌ ከሐዋሳ ውጪ ባሉ ተንቀሳቅሼ እንደ መመልከቴ በሲዳማ ማዕከላዊ ዞን፣ በይርጋለምና በሐዋሳ ምርጫ ክልል መራጮች ቀደም ብለው የተሠለፉ ቢሆንም፣ ከማለዳ 12፡00 ሰዓት ሊጀመር የሚገባው ምርጫ ግን ዘግይቶ እንደጀመረ ታዝቤያለሁ›› ሲሉ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ‹‹በምርጫው ወቅት የነበረው ችግር ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ከሆነም በኋላ ድምፅ ያልሰጡ መራጮች ስላሉ፣ ሠልፍ የሌለባቸው ምርጫ ጣቢያዎች እስከ ሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ ክፍት ሆነው መቆየታቸውን ታዝበናል፤›› ሲሉም ገልጸዋል፡፡ ‹‹መራጮች ተጠቃለው ድምፅ ያልሰጡባቸው ሁለት የሐዋሳ ክልል ምርጫ ጣቢያዎች እስከ ሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ድረስ ቆዩ ተብለን ከምርጫ ቦርድ ታዘናል ብለው የቆዩ የምርጫ አስፈጻሚዎች ነበሩ፤›› ሲሉ ገነት አክለው ገልጸዋል፡፡ በዲጂታል ለምርጫ የተመዘገቡ መራጮችም ምርጫ ጣቢያቸውን ያለማወቅና ሠልፍ ደርሷቸው መዝገባቸው ላይ ስማቸው ሲፈለግ በመታጣቱ፣ ስማቸው የሚገኝበት የምርጫ...
editorial.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-06-04 00:34:07
በምርጫ ማግሥት ሁሉም ነገሮች ወደ መደበኛው የሕይወት እንቅስቃሴ ሊመለሱ የግድ ይላል፡፡ በምርጫ ውጤት ላይ ተመሥርቶ ከሚኖር ውዝግብ አንስቶ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አለመግባባት ከተፈጠረ በሕጋዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ፣ ከተካሄደው ምርጫ የተገኘው ልምድም ሆነ ትምህርት ለወደፊቱ እንዲያገለግል መሠረት እየተጣለ፣ ሆን ተብለውም ሆነ ባለማወቅ የተፈጠሩ ስህተቶች ካሉም እርማት እንዲደረግባቸው ጥብቅ ማሳሰቢያ እየተሰጠ፣ እንዲሁም ከምንም ነገር በላይ የአገር ሰላምና የሕዝብ ደኅንነት ቅድሚያ እያገኘ መደበኛውን እንቅስቃሴ መጀመር አስፈላጊና ተጠባቂ ጉዳይ ነው፡፡ በሕዝብ ድምፅ ተመርጫለሁ የሚል አካልም ከማንም የበለጠ ኃላፊነት እንዳለበት በመገንዘብ፣ በመላ አገሪቱ ሰላማዊ ድባብ የሚፈጠርበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይጠበቅበታል፡፡ የምርጫ አንዱ ዓላማ በዴሞክራሲ መሠረት ላይ የተገነባ ሥርዓት እንዲታነፅ ማገዝ በመሆኑ፣ ቢያንስ ሁሉም መብቶችና ነፃነቶች የሚከበሩበት ሥርዓተ መንግሥት ተመሥርቶ በሰላም ለመተዳደር የሚያስችል ዓውድ መፍጠር ይገባል፡፡ እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ሕዝብ እጅግ የሚያኮሩ የበርካታ ማኅበራዊ እሴቶች ባለቤት ነው፡፡ በሁሉም መልክዓ ምድሮች ውስጥ የሚኖረው ሕዝባችን በሕግ አክባሪነቱ አስደናቂ፣ ለሕግና ለሥርዓት ተገዥ፣ ከላይ እስከ ታች ያሉ አስተዳዳሪዎችንም ሆነ ተሿሚዎች የሚያከብር፣ አገሩ ሰላም ውላ እንድታድር ማንኛውንም ዓይነት መስዋዕትነት ለመክፈል የማያንገራግር፣ እርስ...
Translate »