Etiópia

Melatewerk.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-05-18 02:32:33
ተጨማሪ 9.7 ቢሊዮን ጠይቋል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለምርጫ ሥራው ከለጋሽ አካላት ይገኛል በሚል በዕቅድ ይዞት የነበረው ገንዘብ ባለመገኘቱ፣ አብዛኛው ወጪ በመንግሥት መሸፈኑን አስታወቀ፡፡ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ ለ2018 ዓ.ም. ምርጫ በጀት ያስፈልጋል ተብሎ ተጠይቆ የነበረው 15 ቢሊዮን ብር ቢሆንም፣ ከአጋር ድርጅቶች ይገኛል በሚል ወደ 10.8 ቢሊዮን ብር ዝቅ ያለ በጀት አንደተደለደለለት ገልጸዋል፡፡ በዚህም የበጀት ውስንነት ምክንያት ከዚህ ቀደም ከተመደበለት በተጨማሪ ለቀሪ ሥራዎቹ 9.7 ቢሊዮን ብር አዲስ በጀት በመጠየቅ፣ አጠቃላይ የቦርዱን የምርጫ ወጪ  ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ አሳልፎታል፡፡ ሰብሳቢዋ ይህን የተናገሩት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቦርዱን የፋይናንስ አጠቃቀምና የመጪውን በጀት ዓመት ዕቅድ በተመለከተ ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ በመግለጫቸው ለምርጫው የአጋር ድርጅቶች ድጋፍ እ.ኤ.አ. ከ2022 እና እ.ኤ.አ. 2023 ከነበረው ያነሰ የነበረ በመሆኑ፣ ያንን በመረዳት ለተያዘው ምርጫ ወደ 15 ቢሊዮን ብር ለማሳደግ ታስቦ የነበረ ቢሆንም፣ ድጋፍ ሊመጣ ይችላል በሚል በጀቱ ዝቅ ብሎ መበጀቱን ተናግረዋል፡፡ ‹‹በዚህ ጊዜ ያለው የአጋር ድርጅቶች ድጋፍ በጣም ዝቅተኛ...
Politics-77-1.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-05-17 19:42:02
የጠረፍና ልዩ ልዩ የገጠር አካባቢዎችን የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ 7.5 ሚሊዮን ዶላር ፈንድ መገኘቱ ተነግሯል የግል ዳታ እየሰበሰቡ ያሉና ወደፊትም የሚሰበስቡ የፌዴራል መንግሥትን ጨምሮ ማናቸውም ተቋማት ምዝገባ በማድረግ ፈቃድ እንዲያወጡ፣ የኢትዮጵያ ኮሙዩኒኬሽን ባለሥልጣን አሳሰበ፡፡ ባለሥልጣኑ ማሳሰቢያ የሰጠው፣ የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 1321/2016 ትግበራና አፈጻጸምን በተመለከተ ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የግል ዳታን ለሚሰበስቡና ለሚያቀናብሩ የፌዴራል ተቋማት ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ነው። የኢትዮጵያ ኮሙዩኒኬሽን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሚሊዮን ኃይለ ሚካኤል፣ በአዋጁ መሠረት የግል ዳታ እየሰበሰቡ የሚገኙና ወደፊት የሚሰበስቡ የፌዴራል መንግሥት፣ መንግሥታዊ ያልሆኑና ሌሎች ተቋማት ምዝገባ በማድረግ ፈቃድ እንዲያወጡ ይገደዳሉ ብለዋል። ባለሥልጣኑ አዋጁ ከፀደቀበትና በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ለአንድ ዓመት ከስድስት ወራት ለሚሆን ጊዜ ለሚመለከታቸው ተቋማት የማሳወቅ ሥራው ሲከናወን መቆየቱን፣ ለዚህም ይረዳ ዘንድ ባለሥልጣኑ አዲስ ፕላትፎርም ማዘጋጀቱንና በዚህም መሠረት ተቋማት እየተመዘገቡ ፈቃድ እንዲያወጡ ጥሪ አድርገዋል። ፕላትፎርሙ ‹‹PDP.ECA.ET›› መሆኑን ባለሥልጣኑ በይፋ አስታውቋል። ፕላትፎርሙ ከቀናት በፊት ከመረጃና ኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር (ኢንሳ) የደኅንነት ማረጋገጫ በማግኘቱ፣ ከግንቦት 5 ቀን 2018...
EZEMA.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-05-17 19:40:54
‹‹ፍርድ ቤቱ ውሳኔ የሰጠው የቦርዱን መከራከሪያ ሐሳብ ውድቅ በማድረግ ሆኖ ሳለ ፓርቲው ያቀረበው መረጃ የተሳሳተ ነው››  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ                                                                                                                                         የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ፓርቲ በሐረሪ ክልል ያቀረበው ዕጩ እንዲሰረዝና የክልሉ ተወላጅ የሆነን ዕጩ እንዲያቀርብ በፍርድ ቤት የመወሰኑ ምክንያት የምርጫ ቦርድ ደካማ ክርክር መሆኑን ገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው ምላሽ፣ የሐረሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔ ለመስጠት ሥልጣን እንደሌለው ጭምር መከራከሪያ ሐሳብ ቢያቀርብም፣ ፍርድ ቤቱ ባለመቀበል ውድቅ አድርጎ ውሳኔ ሰጥቶ እያለ ኢዜማ ቦርዱ እንዳልተከራከረ አድርጎ ያቀረበው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑን ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) ‹‹ዴሞክራዊያዊ መብቶች በብሔር ማንነትና በመንግሥት አሉታዊ ተፅዕኖ ውስጥ መውደቃቸው ምርጫውን ችግር ውስጥ ይከታል፤›› በሚል ሐሳብ በወቅታዊ የምርጫ ጉዳዮች ላይ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡                     ፓርቲው በመግለጫው ትኩረት ያደረገበት፣ በሐረሪ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረበውን ዕጩ ሰርዞ፣ የክልሉ ተወላጅ የሆነ ዕጩ እንዲያቀርብ በክልሉ መንግሥት ጠቅላይ ፍርድ ቤት የወንጀልና ፍትሐ ብሔር...
mEKIDES.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-05-17 12:56:47
የጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ሲዘጋጁ የሕክምና ተቋማትንና ሐኪሞችን በአገሪቱ ካሉ ሌሎች የሕክምና ተቋማት የተለዩና የመጠቁ (የበለጡ) አድርጎ በማስመሰልና በመግለጽ ማስተዋወቅን የሚከለክል፣ ሽልማቶችና ዕውቅናዎች በማስታወቂያዎች ሲካተቱም ለሕዝብ ግልጽ ማድረግ የሚገባቸውን ዝርዝር መሥፈርቶች ያካተተ መመርያ ፀደቀ። በጤና ሚኒስትሯ መቅደስ ዳቦ (ዶ/ር) ተፈርሞ የፀደቀው በተያዘው ግንቦት ወር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በሥራ ላይ የዋለው ‹‹የጤና አግልግሎት ማስታወቂያ አዘገጃጀትና ሥርጭት መመርያ ቁጥር 1134/2018›› የጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎችን በአየር ሰዓት፣ በኅትመት ገጽ፣ ወይም በሌሎች ተመሳሳይ መንገዶች የማሠራጫ ዘዴን በመጠቀም፣ ለሕዝብ የሚያደርስ ማንኛውንም ግለሰብ ወይም አካል ‹‹አሠራጭ›› በማለት ይገልጸዋል። ‹‹የማሠራጫ ዘዴ›› ማለት የመገናኛ ብዙኃን፣ ከቤት ውጭ ማስታወቂያ (Outdoor Advertising)፣ የጤና ትምህርት ፕሮግራሞች፣ በቴሌኮሙዩኒኬሽን መስመሮች ላይ የተመሠረቱ የጽሑፍና የድምፅ መልዕክቶች፣ ማኅበራዊ ሚዲያና ድረ ገጾች፣ ዲጂታል ሚዲያ ወይም ማንኛውንም የጤና አገልግሎት ማስታወቂያን ለማሠራጨት የሚያገለግሉ ተመሳሳይ የመገናኛ መስመሮች ማለት መሆኑንም ያትታል። አሠራጮችንና ዘዴዎችን በግልጽና በዝርዝር ያሠፈረው በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች አዘገጃጀትና ሥርጭትን የሚገዛው ይህ አዲስ መመርያ፣ የጤና ተቋማት አገልግሎቶቻቸውን ለሕዝብ ሲያስተዋውቁ ሊከተሏቸው የሚገቡ የሥነ ምግባር ደንቦችንና ግዴታዎችን በዝርዝር ይዟል፡፡ በመላው አገሪቱ በሚገኙ...
Birhanu.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-05-17 12:55:30
የቤቶች ኮርፖሬሽን ላይ ወቀሳ ያቀረቡት ኮሚሽነር ብርሃኑ ‹‹ቤት አይመደብ መኪና አይሰጥ ምን አድርጌ ነው የምሠራው›› ብለዋል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በመጭው ሐምሌ 2018 ለሚጀመረው አዲሱ በጀት ዓመት ያቀረበው የ1.1 ቢሊን ብር በጀት ፍላጎት፣ በመገባደድ ላይ ላለው በጀት ዓመት ከፀደቀለት በጀት በሶስት እጥፍ ያደገና የተጋነነ ነው ሲል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአምስት የዴሞክራሲ ተቋማትን የፋይናንስ አጠቃቀምና የመጪው ዓመት የበጀት ፍላጎት በገመገመበት ወቅት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የቀጣይ ዓመት የበጀት ጥያቄ ላይ ተወያይቷል፡፡ ኮሚሽኑ ለቀጣይ ዓመት በጀት ያቀረበው የተጋነነና በሦስት እጥፍ ያደገ  መሆኑን ያስታወቀው ኮሚቴው፣ 753 ሚሊዮን ብር ከመንግሥት ግምጃ ቤት ለመደበኛ በጀት ፍላጎቱ መጠየቁ ተገልጿል፡፡ በሌላ በኩል ከውጭ ዕርዳታ 402 ሚሊዮን ብር፣ በአጠቃላይ 1.1 ቢሊዮን ብር በጀት ለማግኘት ፍላጎቱን ማቅረቡን አስታውቋል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር ለኮሚሽኑ ባስቀመጠው የበጀት ጣሪያ መሠረት፣ ከመንግሥት ግምጃ ቤት 193 ሚሊዮን ብር ሲሆን፣ አሁን ከጠየቀው ከጣሪያው ጋር ሲተያይ በ560 ሚሊዮን ብር...
Translate »