Etiópia

photo-collage.png-33.png
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-18 14:29:44
“ከውጭ ሆኖ ከመታዘብ፣ ውስጥ ገብቶ በሐሳብ መሟገት ይሻላል ብለን ወደ ምክክሩ ገብተናል” ዓረና ትግራይ ፓርቲ አገራዊ ምክክር ጉባኤው ከመጀመሩ በፊት ሌሎች ፓርቲዎች በምክር ቤታቸው በኩል አጀንዳ ሲያቀርቡ የተለያዩ ምክንያቶችን በማቅረብ ሳይሳተፉ ቀርተው ከነበሩት ፓርቲዎች ሦሥቱ ማለትም እናት፣ ዓረና ትግራይ ለዴሞክራሲ ሉዓላዊነት እና ወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲዎች ወደ አገራዊ ምክክሩ  መግባታቸውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ በምክክሩ ተሳትፎ ያልነበራቸው እነዚህ ፖርቲዎች ወደ ሒደቱ መግባታቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል። እነዚህ ፓርቲዎች ወደ ምክክሩ የገቡት ምክር ቤቱ ባደረገላቸው ጥሪና ለተደጋጋሚ ጊዜ ውይይት ካደረጉ በኋላ  በተደረሰ መግባባት መሆኑን አስረድተዋል። የእነዚህ ፓርቲዎች ወደ ምክክር መግባት ባጠቃላይ በሒደቱ ተሳትፎ የሚያደርጉት የፖለቲካ የፓርቲዎችን ብዛት 60 እንደሚያደርሰው ሰብሳቢው ጨምረው ገልጸዋል። በአገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች በአገራዊ ምክክሩ እንዲሳተፉ ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጸው፣ ያልገቡት ይመጣሉ ብለው እንደሚጠብቁም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕሮፌሰር) በበኩላቸው፣ ዛሬ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የአገራዊ ምክክር ጉባዔ የአራት ቀናት ቆይታን...
photo-collage.png-32.png
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-18 05:46:22
የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲተገብር ተጠይቋል ሕወሓት በትግራይ ክልል ያወጣውን ሕግ የሚያወግዝና የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ ለሙሉ እንዲተገበር የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ዛሬ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓም ተካሄደ። ሰልፉ በትግራይ ክልል የሰላምና ለውጥ ምክር ቤት አስተባባሪነት የተደረገ ነው። የምክር ቤቱ የኮሙዩኒኬሽ አስተባባሪ አቶ ከበደ አሰፋ የህወሓት ቡድን በትግራይ ክልል ያወጣው አፋኝ አዋጅ እንዲነሳና የፕሪቶሪያው ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲከበር ለመጠየቅ የተጠራ ሰልፍ መሆኑን ተናግረዋል። የትግራይ ሕዝብ ዳግም ከተደገሰለት ጦርነት ነፃ እንዲሆን ለፌዴራል መንግሥትና ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጥሪ አቅርበዋል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና የፕሪቶሪያው  ስምምነት አስተባባሪዎች፣ ሥምምነቱ ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር፣ የትግራይ ክልል ሰላም እንዲጠበቅ፣ ሕዝቡም ወደ ልማት እንዲገባና ከዳግም ጥፋት እንዲጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተገኙት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የዚህ ሰልፍ ዋና ዓላማ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዲከበር ለመጠየቅ ነው ብለዋል። From The Reporter Magazine የትግራይ ሕዝብ ሰላም ፈላጊና ወደ ዳግም ጦርነት መግባት እንዳማይፈልግ ተናግረዋል። አቶ ጌታቸው በንግግራቸው በምዕራብ ትግራይ የተያዙ ቦታዎች እንዲመለሱ...
Insurance.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-07-16 06:41:14
ሥራ ሲጀምር ከነበረው 50 ሚሊዮን ዶላር ካፒታል ከግማሽ በላይ መቀነሱን ገለጸ በመንግሥትና በግል ዘርፍ ትብብር የተቋቋመው የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን አክሲዮን ማኅበር፣ ባለፉት አሥር ዓመታት በፀጥታ ችግር ምክንያት ለደረሰ ጉዳት የከፈለውን ጨምሮ፣ 5.2 ቢሊዮን ብር የካሳ ክፍያ መፈጸሙን አስታወቀ፡፡ የኢትዮጵያ ጠለፋ መድን አክሲዮን ማኅበር የተቋቋመበትን አሥረኛ ዓመት በማስመልከት፣ ትናንት ማክሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጥ ነው ይህንን ያስታወቀው፡፡ መንግሥታዊ የሆኑት የኢትዮጵያ መድን ድርጅትና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአክሲዮን ማኅበሩ 41 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ እንዳላቸው፣ ቀሪው 59 በመቶ በግል ባንኮችና ኢንሹራንስ ኩባንያዎች የተያዘ መሆኑን መግለጫውን የሰጡት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ለሜሳ ገልጸዋል፡፡ የንብረትና የሕይወት የጠለፋ መድን እንዲሰጥ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ተሰጥቶት በ2008 ዓ.ም. ሥራ የጀመረው አክሲዮን ማኅበሩ፣ በአሁኑ ወቅት ለ18 የአገር ውስጥና ለ21 የውጭ በድምሩ ለ39 የኢንሹራንስ ኩባንያዎች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን፣ ከ15 ዓለም አቀፍ ኢንሹራንስ ደላሎች (Brokers) ጋር አብሮ እንደሚሠራ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አስረድተዋል፡፡ በየዓመቱ 300 የሚጠጉ የጠለፋ መድን ኮንትራቶችን በመዋዋልና በማደስ እያስተናገደ እንደሆነ፣ ነገር ግን ይህ ቁጥር...
National-dia.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-16 06:40:12
የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከአራት ሺሕ በላይ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት፣ ከ22 ቀናት እስከ አንድ ወር የሚቆይ ጉባዔ፣ ከዛሬ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በይፋ ይጀመራል ። የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕሮፌሰር)፣ ለአገራዊ ምክክር ጉባኤ ተመካካሪዎች ባስተላለፉት መልዕክት፣ ታሪካዊ በሆነው በአገራዊ ምክክር ጉባዔ ለመሳተፍ ሲመጡ፣ የወከሉትን ማኅበረሰብ ድምፅና ምኞት ለማስተጋባት ብቻ ሳይሆን፣ ለአገር የጋራ ዕድልና የወደፊት ዕጣ ፈንታ መሠረት ለመጣል ጭምር በመሆኑ፣ ትከሻቸው  ላይ የወደቀው ኃላፊነት ታላቅና ጥልቅ መሆኑን ገልጸዋል። ‹‹በምክራችሁ የምትደርሱባቸው ውሳኔዎች፣ የምትፈጥሩት መግባባት፣ የምታፀኑት ስምምነት ከዚህ የታሪክ ወቅት ባለፈ ዘልቆ የሚቀጥልና ለሰላማዊት፣ ለዴሞክራሲያዊትና ለተግባባች ኢትዮጵያ መሠረት የሚጥል ነው፤›› ብለዋል። ‹‹ምክክራችሁ በጥበብ፣ በጋራ መከባበርና ለሕዝብ ጥቅም ባላችሁ ፅኑ ቁርጠኝነት እንዲመራ፣ እንዲሁም ለመጪው ትውልድ ብሩህ ነገን የሚያሰናዳ እንዲሆን እመኛለሁ፤›› ሲሉም ተመኝተዋል። የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽነር አምባዬ ኡጋቶ (ዶ/ር)፣ በበኩላቸው የአገራዊ ምክክር ጉባዔው ለኢትዮጵያ የአዲስ ምዕራፍ ጅማሮ ነው ሲሉ ለሪፖርተር ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን በመመካከር ለአገራቸው ትልቅ ሥራ የሚሠሩበት መሆኑን አስረድተዋል። አገራዊ የምክክር ጉባዔው የኢትዮጵያውን መድረክ መሆኑን፣ በዚህም...
Eyob-2.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-07-15 23:57:43
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በንግድ ባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየውን ዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱና የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድን ወደ 16 በመቶ ማሳደጉ፣ በግል ዘርፉ የመበደር አቅምና በሸማቹ ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚያሳድር የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ጠቆሙ። የባንኩ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በበኩላቸው የብድር ዕድገት ገደብ ማንሳት ብቻውን ከብድር ዕድገት ጭማሪ ጋር ተያያዞ በዋጋ ግሽበት ላይ ሊያሳድር የሚችለውን ጫና በመረዳት፣ ተመጣጣኝ ዕርምጃ በመውሰድ የባንኩን የጥብቅ ፖሊሲ አቋም ማስጠበቅ እንደሚያስፈልግ፣ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ግንዛቤ መውሰዱን አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ሰባተኛ ስብሰባ የኢኮኖሚና የፋይናንስ ሁኔታዎች ላይ ግምገማ በማድረግ፣ በቦርዱ ውሳኔ የተሰጠባቸው አምስት ዋና ዋና የፖሊሲ ዕርምጃዎች ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. አሳውቋል። ገዥው ይፋ ከተደረጉት እነዚህ የፖሊሲ ዕርምጃዎች መካከል ዓመታዊ  የብድር ዕድገት ገደብ (Credit Cap) ሙሉ በሙሉ መነሳቱ፣ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ መጠን (NBE Policy Rate) ከነበረበት በአንድ መቶኛ ከፍ በማለት 16 በመቶ ሆኖ አሁን ያለውን የሦስት በመቶኛ ክልል (Band) በነበረበት እንዲቆይ መደረጉ ይገኙበታል። እነዚህ የባንኩ ቦርድ ውሳኔዎች በሸማቹ፣ በግል ዘርፉና...
CArtoon-3.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-15 23:56:13
ከዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን አጋፋሪነት፣ አራት ሺሕ ያህል ተሳታፊዎች በስምንት ዋነኛ አጀንዳዎች ላይ መምከር ይጀምራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ተቀምጠው የሚነጋገሩ የምክክሩ ተሳታፊዎች፣ ከኢትዮጵያ ህልውና በላይ የሚበልጥ ምንም ነገር እንደሌለ በመገንዘብ ኃላፊነታቸውን መወጣት ይገባቸዋል፡፡ በቆይታቸውም ለኢትዮጵያ ችግሮች ማብቂያ የሚያግዙ መፍትሔዎች ላይ ያተኩሩ፡፡ የደሃ አገር ከፍተኛ ሀብት ተከስክሶበት ዝግጅት የተደረገበት ምክክር ውጤቱ ሁሉንም ወገኖች እንዲያግባባ፣ በምክክሩ ወቅት የሚደረጉ የሐሳብ ልውውጦች ኢትዮጵያን ያስቀድሙ፡፡ ‹‹እስከ ዛሬ ድረስ ያለያዩን፣ ያቀያየሙንና ያኮራረፉንን ጉዳዮች በመመካከር እንፈታለን›› ተብሎ በአገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነሩ የተነገረው ከቃል በላይ በተግባር እንዲገለጽ፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ ላይ ያንዣበቡ ሥጋቶች ተጠራርገው እንዲወገዱ የሚያስችሉ ችግር ፈቺ መፍትሔዎች ይፍለቁበት፡፡ የምክክሩ ዋና ዓላማ በፅኑ የታመመች አገርን ለማከም መሆኑን በመገንዘብ፣ ከጎራ ፍላጎቶችና ተፅዕኖዎች ራስን በማላቀቅ እውነተኛ መፍትሔ መፈለግ ይገባል፡፡ ይህ ታሪካዊ ወቅት እንደ ከዚህ ቀደሞቹ መልካም አጋጣሚዎች ተሰነካክሎ እንዳይወድቅ፣ ኢትዮጵያን ለዘመናት እጅና እግሯን አስረው ከያዟት ውስብስብ ችግሮች ማላቀቂያ ለማድረግ መትጋት ተገቢ ነው፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ እየመከረች ነው›› የሚለውን መሪ ቃል የሚመጥን ተግባር ያስፈልጋል፡፡...
IMF.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-07-15 17:24:27
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን በካፒታል ለማጠናከር የሚያስችል ዕቅድ ለማዘጋጀት የጋራ ኮሚቴ መቋቋሙንና ዕቅዱ በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም. መጨረሻ ድረስ እንዲጠናቀቅ መርሐ ግብር መያዙን ይፋ አደረገ። የካፒታል ማጠናከሪያ ዕቅዱ ብሔራዊ ባንክ የወርቅ ግብይት ዘርፉ ላይ በተመሳሳይ ወቅት ያደርጋቸዋል ከተባሉ መዋቅራዊ ማሻሻያዎች ጋር ጎን ለጎን እንደሚከናወን ተጠቁሟል።   ባንኩ ለባህላዊ የወርቅ አምራቾች ከዓለም አቀፍ ገበያ ዋጋ በላይ ሲከፍል የነበረውን የዋጋ ፕሪሚየም ደረጃ በደረጃ ለማስቀረት የሚያስችለው ዕቅድ በመስከረም ወር 2019 ዓ.ም. ከማሻሻያዎቹ መካከል እንደሚገኝበት አይኤምኤፍ ገልጿል። አይኤምኤፍ ትናንት ማክሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ይፋ ያደረገው የኢትዮጵያ የተራዘመ የብድር (Extended Credit Facility (ECF)) ስምምነት መርሐ ግብር አምስተኛ ግምገማ ሰነድ እንደሚያስረዳው፣ ብሔራዊ ባንክ የፕሪምየም ክፍያውን በተያዘው በጀት ዓመት ደረጃ በደረጃ ወደማቆም የሚሸጋገረው የወርቅ ንግዱን ቀስ በቀስ ወደ ግል ዘርፉ ለማሸጋገር በያዘው ሰፊ የዘርፉ ማሻሻያ ዕቅድ በኩል መሆኑና በዚህም የባንኩን የፋይናንስ ኪሳራዎች (Losses) በመቀነስ፣ የሒሳብ ሚዛኑን (Balance Sheet) ለማጠናከር መታሰቡን አስታውቋል፡፡ በዓለም አቀፉ ተቋም የግምገማ ሰነድ ላይ የተጠቀሰው የባንኩ የ2017 በጀት ዓመት...
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-15 17:23:17
ጥናቱ እ.ኤ.አ. ከ2008 እስከ 2023 ድረስ 207.7 ቢሊዮን ዶላር ማጣቷን ያሳያል የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር ከአንድ ሳምንት በፊት ይፋ ያደረጉት ጥናት፣ ኢትዮጵያ በየዓመቱ በቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ በንግድ ማጭበርበርና በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ምክንያት እንደምታጣ አመላከተ፡፡ የሁለቱ ተቋማት ተመራማሪዎች በጋራ ያቀረቡትና ውይይት የተደረገበት ጥናት  ከ2008 እስከ 2023 በአጠቃላይ የንግድ ሥርዓቱ፣ እንዲሁም እ.ኤ.አ. በ2025 ደግሞ የተመረጡ አስመጪዎች፣ ላኪዎችና አምራቾች በንግድ ማጭበርበር ላይ በማተኮር የተሠራ ነው ተብሏል፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2008 እስከ 2013 በነበሩት ዓመታት 207.7 ቢሊዮን ዶላር የንግድ ማጭበርበር መፈጸሙን የሚያሳይ ሲሆን፣ ይህ በአማካይ በየዓመቱ 12.9 ቢሊዮን ዶላር የንግድ ማጭበርበር እንደተፈጸመ ያስረዳል፡፡ ይህም በዋነኝነት በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በውጭ ምንዛሪ እጥረት፣ በደካማ የንግድ ሥርዓት፣ በአገር ውስጥ የሀብት አሰባሰብ ሥርዓት መበላሸት ምክንያት የተፈጠረ ነው የሚለው ጥናቱ፣ ከ85 በመቶ በላይ ለሚሆነው የንግድ ማጭበርበር ለሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ምክንያት መሆኑን ይጠቅሳል፡፡ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ሸቀጦችን ዋጋ በማናር (Over Invoicing) ከ113.8 ቢሊዮን እስከ 119 ቢሊዮን ዶላር ሳይጠፋ እንዳልቀረ የሚያስረዳው ጥናቱ፣ የሸቀጦችን ዋጋ ማናር ወደ ውጭ የሚደረገውን...
Eyob-11.jpg
Etiópia, Ethioobserver, Inglês/Amárico
2026-07-15 10:53:54
 የወርቅ ግዥን ወደ ንግድ ባንኮች ለማዘዋወር ጥናት እየተደረገ ነው ተብሏል የወርቅ ሻጮች ለንግድ ባንኮች ወርቅ እንዲያቀርቡ ግፊት እየተደረገ መሆኑም ተጠቅሷል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የአገሪቱ የመጀመሪያው የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ፣ በመጪው አንድ ወር ውስጥ ተመርቆ ሥራ እንደሚጀምር አስታወቁ። ገዥው ይህንን የገለጹት የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በሰባተኛ ስብሰባው የገመገማቸውን የኢኮኖሚና የፋይናንስ ሁኔታዎች፣ ያቀረባቸውን ምክረ ሐሳቦችና የብሔራዊ ባንክ ቦርድ ያፀደቃቸውን የፖሊሲ ውሳኔዎች አስመልክቶ ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ለመገናኛ ብዙኃን ማብራሪያ ሲሰጡ ነው። ከአፍሪካ አልፎ ከዚያ በላይ በግዙፍነቱ የሚጠቀስ የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ (ሪፋይነሪ) ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት እዮብ (ዶ/ር)፣ ፋብሪካው በመጪው አንድ ወር ውስጥ ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲገባ፣ ለአገሪቱ የወርቅ ገበያ እጅግ ከፍተኛ አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል። የአገር ውስጥ የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ወጪን በከፍተኛ ደረጃ ከመቀነሱም በላይ፣ ቀደም ሲል ወርቅ ወደ ውጭ በመላክ እንዲነጠር ተደርጎ ከዚያ በኋላ ለሌሎች ክምችት በዶላር የመሸጠን አሠራር ሙሉ ለሙሉ የሚያስቀር ነው ብለዋል። በመሆኑም ፋብሪካው ለኢትዮጵያ የወርቅ ገበያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው ትልቅ አቅም ሊሆን ይችላል ሲሉ...
1784111729570.jpg
Etiópia, Ethiopian Reporter, Amárico
2026-07-15 10:52:45
ላለፉት አራት ዓመታት በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ልዩ ዝግጅት የተገኘውን አገራዊ የምክክር ዕድል በኃላፊነት ስሜት በመጠቀም፣ ግጭትና ስቃይ ማብቃት አለበት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር) ዛሬ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓም የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ጉባኤ በአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል ሲጀመር ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ጥሪ አቀረቡ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው፣ ይህ ምክክር በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ የገዘፈ ዓላማ ያለውና ለአፍሪካ ተምሳሌት የሚሆን መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። አገራዊ ጉባዔው የትላንትን ችግር ፈትቶ ለነገ መሠረት ለማኖር የሚያስችል መሆኑን፣ ታሪክን ለመፃፍ ደግሞ ብዕርና ብራና የሚሰጥ በመሆኑ፣ አጋጣሚውን በአግባቡ በኃላፊነት ስሜት መጠቀም ይገባል ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል። ይህን ዕድል በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ሰላም፣ የተሻለ ኑሮ እንዲኖር የሚያስችል ነው ሲሉ ተናግረዋል። እንደ አገር ይቅርታን፣ እርቅን፣ ምክክርን እንትከል ሲሉም አክለዋል።ተመካካሪዎች ለዛሬ ሳይሆን ለነገ፣ ለራሳቸው ሳይሆን ለልጆቻቸው እንዲመክሩም አሳስበዋል። ውይይቱ የሚሳካው ተመካካሪዎች ለእኔ ሳይሆን ለእኛ፣ ለሰፈሬ ሳይሆን ለአገሬ ካሉ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም አንዱ ሌላኛው የሚያነሳውን ሐሳብ ሊያከብር ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል። “አገርን ስንገነባ ያልነበሩ፣ ስንጣላ የሚኖሩ አሞራዎችን በቃ...
Translate »